Monday, 10 August 2020 00:00

ትራምፕ በተሳሳተ የኮሮና መረጃ ከትዊተርና ፌስቡክ ታገዱ

Written by 
Rate this item
(1 Vote)

  ታዋቂዎቹ የማህበራዊ ድረ ገጾች ፌስቡክና ትዊተር ከኮሮና ቫይረስ ጋር በተያያዘ የተሳሳተ መረጃ አሰራጭተዋል በሚል በአሜሪካው ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ ድረ ገጾች ላይ የእገዳ እና መረጃ የማንሳት እርምጃዎችን እንደወሰዱ አሶሼትድ ፕሬስ ዘግቧል፡፡
ሁለቱ ኩባንያዎች በትራምፕ ላይ እርምጃ ለመውሰድ የወሰኑት ህፃናት የበሽታ መከላከል አቅማቸው ከፍተኛ በመሆኑ ለኮሮና ቫይረስ አይጋለጡም የሚል የተሳሳተና አደገኛ መረጃ በማሰራጨታቸው መሆኑን የጠቆመው ዘገባው፣ ፕሬዚዳንቱ በፌስቡክና ትዊተር ላይ አድርገውት የነበረው መረጃ በኩባንያዎቹ በአፋጣኝ እንዲነሳ መደረጉንም አመልክቷል፡፡
ትዊተር ፕሬዚዳንት ትራምፕ ከኮሮና ጋር በተያያዘ የለቀቁትን የተሳሳተ መረጃ የያዘ አጭር ቪዲዮ እስኪያነሱት ድረስ ለምርጫ ቅስቀሳ የሚጠቀሙበትን ይፋዊ የትዊተር ገፃቸውን ማገዱን ያስታወቀ ሲሆን ፌስቡክ በበኩሉ፤ በትራምፕ ገጽ ላይ የተለቀቀው ቪዲዮ ከበሽታ መከላከል ጋር በተያያዘ ሀሰተኛ መረጃ የያዘ እንዲሁም የመተዳደሪያ ደንብና ፖሊሲውን የሚጥስ በመሆኑ መረጃውን ማንሳቱን አስታውቋል፡፡

Read 3359 times