Monday, 03 August 2020 00:00

ባለፈው አመት ከ1ሺህ 750 በላይ ስደተኞች በሜዲትራኒያን ሞተዋል

Written by 
Rate this item
(0 votes)

  በ2019 የፈረንጆች አመት ብቻ በአፍሪካ በኩል ሜዲትራኒያን ባህርን አቋርጠው ወደአውሮፓ አገራት ለመግባት በጉዞ ላይ የነበሩ ከ1ሺህ 750 በላይ ስደተኞች በጉዞ ላይ ሳሉ ለሞት መዳረጋቸውን ተመድ አስታውቋል፡፡
የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የስደተኞች ከፍተኛ ኪሚሽን ከሰሞኑ ባወጣው አዲስ ሪፖርት እንዳለው፣ በአመቱ በወር ቢያንስ 72 ስደተኞች በሰሃራ በረሃ እና በሊቢያ በኩል አድርገው ሜዲትራኒያን ባህርን በመሻገር ወደ አውሮፓ አገራት ለመግባት ሲሞክሩ ለሞት ተዳርገዋል፡፡
ስደተኞቹ ህገወጥ የሰዎች አዘዋዋሪዎች፣ የድንበር ጠባቂዎች፣ ታጣቂዎችና ፖሊሶችን ጨምሮ በተለያዩ አካላት ከፍተኛ የሰብዓዊ መብቶች ጥሰቶችና የተለያዩ አካላዊ ጥቃቶች እንደሚደርሱባቸው የጠቆመው ሪፖርቱ፣ የጥቃት መጠኑ ከጊዜ ወደ ጊዜ በከፍተኛ ሁኔታ ማደጉንም አብራርቷል፡፡


Read 3958 times