Sunday, 08 March 2020 00:00

የፀሐፍት ጥግ

Written by 
Rate this item
(2 votes)

 • ‹‹…የብሔር ፖለቲካ የተፈጠረውና እንደ ጎላ ድስት ከስሎ የወጣው በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ግቢ ውስጥ ነው፡፡ ስለዚህ በተነሳ ቁጥር ዋለልኝ መኮንን ይጠቀሳል:: የዋለልኝ ሀሳብ ጥሩ ቢሆንም አገሪቷ መከፋፈል የጀመረችው እሱ ባመጣው ሀሳብ ነው፡፡…››
• ‹‹…ገዳም የገባ መነኩሴ የሚፈተነውም በዝምታ ወቅት ነው፡፡ ገዳም የገባ መናኝ መሆኑ የሚረጋገጠው አርምሞ ላይ ሲደርስ ብቻ ነው፡፡ ምክንያቱም ሁሉን
አውቆ ንቆ ሲተው ነው፡፡ አርምሞ ላይ ለመድረስም ፈታኝ ነው፡፡ ለዚህም ድንጋይ እስከ መንከስ የደረሱ መናኞች አሉ፡፡…››
• ‹‹…የዕውቀት መሰረት በመማር ብቻ አይመጣም፡፡ ብዙ ያልተማሩ ምሁሮች አሏት - አገራችን፡፡ አድዋ የዘመቱትን መጥቀስ ይቻላል፡፡ ከዛ በፊትም ለሙሴ
አመራር ያስተማረውን የምድያሙን ካህን ዮቶርን መጥቀስ ይቻላል፡፡…››
• ‹‹…ወንጀልን ስትፈፅመው አትፀፀትም:: ከዛ በኋላ ግን ወንጀሉን እንዴት ልደብቀው ትላለህ… ነፃ ሆነህ መኖር ትፈልጋለህ! ወንጀሉን የሚያጣራ አካል እንዳይመጣ ትፀልያለህ! ሆኖም ለማን እንደምትፀልይ አይገባህም፡፡ ፈጣሪን ትረግመዋለህ፡፡…››
• ‹‹…በተሰበክነው ስብከት መሰረት እኛ በህብረት መሥራት አንችልም፡፡ በግለሰብ ደረጃ ግን እንችላለን፡፡ ሩጫ እንችላለን:: እግር ኳስ ግን አንችልም፡፡ ሜዳ
ታጥቶ አይደለም፡፡ በህብረት መስራት ስለማንችል ነው፡፡ ብሔር ሆነን የሰራነው አንድም ቅርስ የለም፡፡ ብሔር ሆነን ለእኛ የማይታገሉ መሪዎች እንመርጣለን እንጂ ምን እንደሰሩ አንጠይቅም፡፡ ብንጠይቅም አገሪቷ ደሃ ናት ይሉናል፡፡…››
(ከደራሲ ይስማዕከ ወርቁ ‹‹ደህንነቱ›› መጽሐፍ የተወሰደ

Read 1586 times