• ‹‹…የብሔር ፖለቲካ የተፈጠረውና እንደ ጎላ ድስት ከስሎ የወጣው በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ግቢ ውስጥ ነው፡፡ ስለዚህ በተነሳ ቁጥር ዋለልኝ መኮንን ይጠቀሳል:: የዋለልኝ ሀሳብ ጥሩ ቢሆንም አገሪቷ መከፋፈል የጀመረችው እሱ ባመጣው ሀሳብ ነው፡፡…››
• ‹‹…ገዳም የገባ መነኩሴ የሚፈተነውም በዝምታ ወቅት ነው፡፡ ገዳም የገባ መናኝ መሆኑ የሚረጋገጠው አርምሞ ላይ ሲደርስ ብቻ ነው፡፡ ምክንያቱም ሁሉን
አውቆ ንቆ ሲተው ነው፡፡ አርምሞ ላይ ለመድረስም ፈታኝ ነው፡፡ ለዚህም ድንጋይ እስከ መንከስ የደረሱ መናኞች አሉ፡፡…››
• ‹‹…የዕውቀት መሰረት በመማር ብቻ አይመጣም፡፡ ብዙ ያልተማሩ ምሁሮች አሏት - አገራችን፡፡ አድዋ የዘመቱትን መጥቀስ ይቻላል፡፡ ከዛ በፊትም ለሙሴ
አመራር ያስተማረውን የምድያሙን ካህን ዮቶርን መጥቀስ ይቻላል፡፡…››
• ‹‹…ወንጀልን ስትፈፅመው አትፀፀትም:: ከዛ በኋላ ግን ወንጀሉን እንዴት ልደብቀው ትላለህ… ነፃ ሆነህ መኖር ትፈልጋለህ! ወንጀሉን የሚያጣራ አካል እንዳይመጣ ትፀልያለህ! ሆኖም ለማን እንደምትፀልይ አይገባህም፡፡ ፈጣሪን ትረግመዋለህ፡፡…››
• ‹‹…በተሰበክነው ስብከት መሰረት እኛ በህብረት መሥራት አንችልም፡፡ በግለሰብ ደረጃ ግን እንችላለን፡፡ ሩጫ እንችላለን:: እግር ኳስ ግን አንችልም፡፡ ሜዳ
ታጥቶ አይደለም፡፡ በህብረት መስራት ስለማንችል ነው፡፡ ብሔር ሆነን የሰራነው አንድም ቅርስ የለም፡፡ ብሔር ሆነን ለእኛ የማይታገሉ መሪዎች እንመርጣለን እንጂ ምን እንደሰሩ አንጠይቅም፡፡ ብንጠይቅም አገሪቷ ደሃ ናት ይሉናል፡፡…››
(ከደራሲ ይስማዕከ ወርቁ ‹‹ደህንነቱ›› መጽሐፍ የተወሰደ
Published in
ጥበብ
Latest from Administrator
- የእስራኤል እና የኢራን ፍጥጫ
- Insights on Israel's Response: Interview with Mr. Tomer Bar-Lavi, Chargé d’Affaires at the Embassy of Israel to Ethiopia
- Barr, a vocal Trump critic, says he will ‘support the Republican ticket’ in November
- Iran president warns of ‘massive’ response if Israel launches ‘tiniest invasion’
- "አልሞቷል" ፊልም ዛሬ በዓለም ሲኒማ ይመረቃል