Monday, 24 February 2020 09:55

‹‹የሚዲያና የሕዝብ ግንኙነት አሰራር›› መጽሐፍ ለንባብ በቃ

Written by 
Rate this item
(14 votes)


         በአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ መምህርና ተመራማሪ በሆኑት አቶ መኮንን ተካ የተዘጋጀው መጽሐፍ በሁሉም የመጽሐፍት መደብሮች ለገበያ ቀርቧል፡፡ መምህር መኮንን ተካ የጋዜጠኝነትና ተግባቦት መምህር ሲሆኑ ከዚህ መጽሐፍ በተጨማሪ ዝናቸው ከፍ ባሉ አለም አቀፍ የምርምር ጆርናሎች የተለያዩ
የምርምር መጣጥፎችን አበርክተዋል፡፡ ለ3ኛ ጊዜ የታተመና ጠለቅ ያለ ማሻሻያ የተደረገበት ይህ መጽሐፍ የሚከተሉትን ጉዳዮች ይዳስሳል፡-
- የሚዲያን ተጽዕኖና የማህበረሰብ ግንኙነትን በተመለከተ በቂ መረጃ ያቀርባል፣
- ስለ ሚዲያና ህዝብ ግንኙነት ዝርዝር ፍልስፍናዎችንና የአሠራር መርሆዎችን ይተነትናል፣
- ለተለያዩ የሚዲያ ዘውጐች የሚሆኑ ዘገባዎች እንዴት መሰናዳት እንዳለባቸው ያብራራል፣
- የሃሳብ ነፃነትን፣ የሚዲያ ህጐችንና የጋዜጠኝነት አተገባበር ምን መምሰል እንዳለበት ሃሳብ ያቀርባል፣
- በሀገራችን የሚዲያና የህዝብ ግንኙነት አተገባበር ላይ በንድፈ - ሀሳባዊ ቅኝት በመታገዝ አውዳዊ እውቀትን ያስጨብጣል፡፡
- መረጃና እውቀት እንዴት በጋዜጠኝነት መደራጀት እንዳለበት ያብራራል፣
- ከህትመትና ከአርትኦት ጋር በተገናኙ ርእሰ ጉዳዮች፣ ከጋዜጠኝነት አተገባበር አንፃር በቂ መረጃ ያቀርባል፡፡


Read 11917 times