ጄፍ ቤዞስ 10 በመቶ ሃብታቸውን ለአየር ንብረት ለውጥ ድጋፍ እንደሚያደርጉ ተናግረዋል
የናሚቢያ ቀዳማዊት እመቤት ሞኒካ ጄኒጎስ ከዚህ አለም በሞት ሲለዩ 3 ሚሊዮን ዶላር የሚገመት ሃብታቸው በሙሉ ለበጎ አድራጎት እንዲውል መወሰናቸውን እንዲሁም የአለማችን ቁጥር አንድ ቢሊየነር ጄፍ ቤዞስ ከአጠቃላይ ሃብታቸው 10 በመቶ ያህሉን ወይም 10 ቢሊዮን ዶላር ለአየር ንብረት ለውጥ መከላከል ተግባር እንደሚለግሱ መናገራቸው ተዘግቧል፡፡
በአገራቸው የጾታ ልዩነትን ማጥፋትን ጨምሮ የተለያዩ የበጎ ምግባር ስራዎችን በመስራት የአፍሪካውያን ቀዳማዊ እመቤቶችን ገጽታ ለመገንባት እየጣሩ የሚገኙት ሞኒካ ጄኒጎስ፤ሃብታቸውን ለበጎ ምግባር ለማዋል መወሰናቸውን እንዳስታወቁ ዘገባው አመልክቷል፡፡ በሌላ ዜና ደግሞ አሜሪካዊው የአለማችን ቁጥር አንድ ቢሊየነር ጄፍ ቤዞስ፤ ከአጠቃላይ ሃብታቸው 10 በመቶ ያህሉን ወይም 10 ቢሊዮን ዶላር ለአየር ንብረት ለውጥ መከላከል ተግባር እንደሚለግሱ ባለፈው ሰኞ ማስታወቃቸው ተነግሯል፡፡
የአማዞኑ መስራችና ዋና ስራ አስፈጻሚ ጄፍ ቤዞስ አዲስ ባቋቋሙት ቤዞስ አርዝ ፈንድ የተባለ ፋውንዴሽን አማካይነት በአለማቀፍ ዙሪያ ለሚደረጉ ከአየር ንብረት ለውጥ ጋር የተያያዙ እንቅስቃሴዎች የ10 ቢሊዮን ዶላር ድጋፍ እንደሚያደርጉ ነው የተናገሩት፡፡ የገንዘብ ድጋፉ ከሚደረግላቸው መካከል በአየር ንብረት ለውጥ ዙሪያ የሚሰሩ ተመራማሪዎች፣ አክቲቪስቶች፣ መንግስታዊ ያልሆኑ ድርጅቶች እንደሚገኙበት የዘገበው ፎርብስ መጽሄት፣ ተፈጥሮን በመንከባከብ ላይ ትኩረት ላደረጉ ቅድሚያ ይሰጣል መባሉንም ገልጧል፡፡ የአለማችን ቁጥር አንድ ባለጸጋ የሆኑት ጄፍ ቤዞስ አጠቃላይ የተጣራ ሃብታቸው 129.9 ቢሊዮን ዶላር እንደሚደርስም ዘገባው አክሎ አስታውሷል፡፡
Saturday, 22 February 2020 12:27
የናሚቢያ ቀዳማዊት እመቤት ሙሉ ሃብታቸውን ለበጎ አድራጎት እንደሚሰጡ አስታወቁ
Written by Administrator
Published in
ከአለም ዙሪያ
Latest from Administrator
- የእስራኤል እና የኢራን ፍጥጫ
- Insights on Israel's Response: Interview with Mr. Tomer Bar-Lavi, Chargé d’Affaires at the Embassy of Israel to Ethiopia
- Barr, a vocal Trump critic, says he will ‘support the Republican ticket’ in November
- Iran president warns of ‘massive’ response if Israel launches ‘tiniest invasion’
- "አልሞቷል" ፊልም ዛሬ በዓለም ሲኒማ ይመረቃል