Print this page
Saturday, 15 February 2020 12:48

የልጆች ጥግ

Written by 
Rate this item
(2 votes)

   ውድ ልጆች፡- ከቤተሰብ አባላት ወይም ከክፍል ጓደኞቻችሁ አንድ ነገር መውሰድ ስትፈልጉ ፈቃዳቸውን መጠየቅ እንዳለባችሁ አትዘንጉ፡፡ ለምሳሌ፡- መጽሐፋቸውን ወስዳችሁ መጠቀም ከፈለጋችሁ፣ “መፅሐፍህን መዋስ እችላለሁ?” ብላችሁ በትህትና ጠይቁ፡፡ እህታችሁ ወይም ወንድማችሁ አሊያም ጓደኛችሁ መጽሐፋቸውን እንድትዋሱ ከፈቀዱላችሁ ታዲያ ንብረታቸውን በእንክብካቤ መያዝ ይኖርባችኋል፡፡ ገፆቹ መቀደድ የለባቸውም፡፡ ሽፋኑ ላይ ለስላሳ ወይም ጁስ ወይም ሌላ ነገር እንዳይፈስበት መጠንቀቅ ይገባችኋል፡፡  
መጽሐፉን ተጠቅማችሁ ወይም አንብባችሁ ስትጨርሱ፣ ወዲያውኑ መመለስ አለባችሁ፡፡ “አመሰግናለሁ! መጽሐፉ በጣም ጠቅሞኛል ወይም ወድጄዋለሁ” ከሚል ምስጋና ጋር መሆን ይገባዋል፡፡ እንዲያ ሲሆን ወደፊትም ሌሎች ነገሮችን በቀላሉ ሊያውሷችሁ ይችላሉ፡፡  
ውድ ልጆች፡- እናንተም ታዲያ መጽሐፋችሁን ወይም ጌማችሁን አሊያም ሌላ ነገር አውሱን ስትባሉ በደስታ መፍቀድ ይገባችኋል፡፡ የሌሎችን እየተዋሱና እየተጠቀሙ የራስን መደበቅ ወይም አለማዋስ ትክክል አይደለም፡፡ የቤተሰብ አባላትም ይሁኑ ጓደኞች ይከፉባችኋል፡፡
ሁልጊዜም ወላጆቻችሁንና ታላላቆቻችሁን ማክበርና ትዕዛዛቸውን ማክበር አለባችሁ፡፡ አስተማሪዎቻችሁንም ውደዷቸው፤ አክብሯቸው፡፡ በአስተማሪዎች ላይ መሳቅና ማሾፍ መጥፎ ተግባር ነው፡፡ የዕውቀት አባቶችና እናቶች ስለሆኑ መከበር አለባቸው፡፡   
እደጉ! እደጉ! እደጉ!

Read 1183 times
Administrator

Latest from Administrator