የአሜሪካ የፌደራል ምርመራ ቢሮ ኤፍቢአይ ባለፈው አመት ሪፖርት ከተደረጉለት የኢንተርኔት ጥቃቶች ብቻ ወንጀለኞች 3.5 ቢሊዮን ዶላር መዝረፋቸውን እንዳስታወቀ ሲኤንኤን ዘግቧል፡፡
ባለፈው የፈረንጆች አመት 2019 ብቻ፣ በ48 የተለያዩ የአለማችን አገራት ውስጥ ከሚገኙ 467 ሺህ 361 ግለሰቦችና የንግድ ተቋማት፣ የኢንተርኔት ጥቃት ደርሶብናል የሚል አቤቱታ እንደቀረበለት የገለጸው ኤፍቢአይ፤ በአመቱ የኢንተርኔት ወንጀለኞች በድምሩ 3.5 ቢሊዮን ዶላር ያህል መዝረፋቸውንም አስታውቋል፡፡
የኢንተርኔት ወንጀለኞች ግለሰቦችንና የንግድ ተቋማትን የሚያጠቁባቸው መንገዶች ከጊዜ ወደ ጊዜ እየረቀቁና እየተወሳሰቡ መጥተዋል ያለው ቢሮው፤ ተጠቃሚዎችም ወንጀለኞችን ከጤነኞች ለመለየት የሚቸገሩበት ሁኔታ ተፈጥሯል ብሏል፡፡
ትክክለኛ በሚመስሉ ድረገጾችና የኤሌክትሮኒክ መልዕክት አድራሻዎች ተጠቅመው ከግለሰቦችና ተቋማት ጋር ግንኙነት የሚፈጥሩና ግላዊ መረጃዎችን የሚመነትፉ እንዲሁም ኮምፒውተሮችን ከአገልግሎት ውጭ የሚያደርጉ ወንጀለኞች እየበዙ መምጣታቸውንም ቢሮው ባወጣው ሪፖርት አመልክቷል፡፡
የግለሰቦችንና የንግድ ተቋማትን ኮምፒውተሮች በመዝጋትና ከጥቅም ውጭ በማድረግ፣ የተዘጋውን ለመክፈት ይህን ያህል ገንዘብ ክፈሉን እያሉ የሚደራደሩ የኢንተርኔት ጥቃት አድራሾች፣ ባለፈው የፈረንጆች አመት 2019 ብቻ፣ 8.9 ሚሊዮን ዶላር ያህል ገቢ ማግኘታቸውንም አክሎ ገልጧል፡፡
Published in
ከአለም ዙሪያ
Latest from Administrator
- የእስራኤል እና የኢራን ፍጥጫ
- Insights on Israel's Response: Interview with Mr. Tomer Bar-Lavi, Chargé d’Affaires at the Embassy of Israel to Ethiopia
- Barr, a vocal Trump critic, says he will ‘support the Republican ticket’ in November
- Iran president warns of ‘massive’ response if Israel launches ‘tiniest invasion’
- "አልሞቷል" ፊልም ዛሬ በዓለም ሲኒማ ይመረቃል