Print this page
Monday, 10 February 2020 00:00

የሌሴቶ ቀዳማዊት እመቤት በነፍስ ማጥፋት ተከሰሱ

Written by 
Rate this item
(1 Vote)

የሌሴቶ ቀዳማዊት እመቤት ጣውንታቸውን ገድለዋል በሚል በነፍስ ማጥፋት ወንጀል ክስ እንደተመሰረተባቸው ዘ ጋርዲያን ባለፈው ረቡዕ ባወጣው ዘገባ አስነብቧል፡፡
የአገሪቱ ጠቅላይ ሚኒስትር ቶማስ ታባኔ የቀድሞ የትዳር አጋር የነበሩት ሊፖሊዮ ታባኔ በ2017 መገደላቸውን ያስታወሰው ዘገባው፣ በግድያው ውስጥ እጃቸው አለበት የተባሉት የወቅቱ የአገሪቱ ቀዳማዊት እመቤት ሜሳህ ታባኔ ባለፈው ማክሰኞ በፖሊስ ቁጥጥር ስር መዋላቸውንና በነፍስ ማጥፋት ሊከሰሱ መሆኑን አመልክቷል፡፡
ፖሊስ ከግድያው ጋር በተያያዘ ምርመራ መጀመሩን ተከትሎ ከእስር ለማምለጥ አገር ጥለው ወደ ደቡብ አፍሪካ ጠፍተው የነበሩት ቀዳማዊት እመቤት ሜሳህ ታባኔ፣ ባለፈው ማክሰኞ ወደ አገራቸው እንደተመለሱ በፖሊስ ቁጥጥር ስር መዋላቸውንም ዘገባው ገልጧል፡፡
ጠቅላይ ሚኒስትር ቶማስ ታባኔ የቀድሞ የትዳር አጋራቸው ሊፖሊዮ ታባኔ ከመኖሪያ ቤታቸው አቅራቢያ ተገድለው ከተገኙ ከሁለት ወራት በኋላ ከአሁኗ ቀዳማዊት እመቤት ሜሳህ ታባኔ ጋር ትዳር መመስረታቸውን ያስታወሰው ዘገባው፣ በግድያው የተጠረጠሩት ቀዳማዊ እመቤቷ በቅርቡ ፍርድ ቤት ይቀርባሉ ተብሎ እንደሚጠበቅም አመልክቷል፡፡

Read 3251 times
Administrator

Latest from Administrator