ፍለጋ
ደስታን ስፈልግ ነው
ደስታዬ የራቀኝ
ፍቅርን ስሻ ነው
ፍቅር የጠፋብኝ
ሰላምን ሳስስ ነው
ሰላሜን ያጣሁት
ፍላጐቴን ስገድል
ሁሉን አገኘሁት፡፡
(2011፤ዳዊት ፀጋዬ)
_________
ሀይል
“ክፉና መልካም
ከልዑል አፍ ይወጣል”
ተብሎ ተጽፏል
እናም
በዚህች አጽናፍ ዓለም
ሁለት ሀይል የለም
ብቸኛው ሀይል
እግዚአብሔር ነው እርሱ
ሰይጣን የሚሆነውም
እግዚአብሔር ራሱ፡፡
(2011፤ዳዊት ፀጋዬ)
Published in
የግጥም ጥግ