በቀን 1 ፓኮ የሚያጨስ ሰው፣ በአመት 18 ሺህ ዶላር ያወጣል
ሲጋራ በዜጎች ጤንነት ላይ እያደረሰ ያለው ጉዳትና የሲጋራ አጫሾች ቁጥር መበራከቱ ያሳሰበው የአውስትራሊያ መንግስት፤ በሲጋራ ላይ በአለም እጅግ ውዱን ዋጋ ሊጥል ያቀደ ሲሆን ዕቅዱ ከተሳካ በአገሪቱ የአንድ ፓኮ ሲጋራ ዋጋ 50 ዶላር ሊደርስ እንደሚችል ተዘግቧል፡፡
የአገሪቱ መንግስት በሲጋራ የመሸጫ ዋጋ ላይ የ12.5 በመቶ ጭማሪ በማድረግ፣ አንድ ፓኮ ሲጋራ 50 ዶላር እንዲደርስ ዝግጅት እያደረገ እንደሚገኝ የዘገበው ዴይሊ ሜይል፤ የዋጋ ተመን ማስተካከያው ከመጪው መስከረም ወር ጀምሮ ተግባራዊ ይደረጋል ተብሎ እንደሚጠበቅ አመልክቷል፡፡
የዋጋ ማስተካከያው ተግባራዊ የሚደረግ ከሆነ በቀን አንድ ፓኬት ሲጋራ የሚያጨስ አውስትራሊያዊ፤ በአመት በአማካይ 18 ሺህ ዶላር ለማውጣት እንደሚገደድም ዘገባው ጠቁሟል፡፡
Published in
ከአለም ዙሪያ