Saturday, 11 January 2020 12:10

ልጆቹን በ120 ዶላር ሊሸጥ የሞከረ ሞዛምቢካዊ ታሰረ

Written by 
Rate this item
(0 votes)

  ማኒካ በተባለችው የሞዛምቢክ ግዛት ሁለት ሴት ልጆቹን በ120 ዶላር ለመሸጥ ሲስማማ ነበር የተባለው አባት በፖሊስ ቁጥጥር ስር መዋሉን አፍሪካን ኒውስ ከትናንት በስቲያ ባወጣው ዘገባ አስነብቧል፡፡
የ49 አመት ዕድሜ እንዳለው የተነገረለትና ባለፈው ቅዳሜ በፖሊስ ቁጥጥር ስር የዋለው ሞዛምቢካዊው አባት፣ ድርጊቱን ለመፈጸም ያነሳሳው የገንዘብ እጥረት እንደሆነና ልጆቹን ሽጦ በሚያገኘው ገንዘብ ከሌላ ሰው የተበደረውን የ65 ዶላር ዕዳ ለመክፈል አቅዶ እንደነበር ዘገባው አብራርቷል፡፡
ግለሰቡ የስድስት እና የዘጠኝ አመት ዕድሜ ያላቸውን ሴት ልጆቹን ለመሸጥ ሲደራደር በአካባቢው ሰዎች ጥቆማ በፖሊስ ቁጥጥር ስር መዋሉን የጠቆመው ዘገባው፣ ልጆቹን ለመግዛት ዋጋ ሲደራደር የነበረው ገዢም መታሰሩን አመልክቷል፡፡
በሞዛምቢክ ህጻናትንና ሴቶችን በአገር ውስጥና ለጎረቤት አገራት ለወሲብና ለባርነት የመሸጥ ተግባር ስር የሰደደ ነው ያለው ዘገባው፣ ግለሰቡ በቅርቡ ፍርድ ቤት ቀርቦ ቅጣት ይጣልበታል ተብሎ እንደሚጠበቅም ጠቁሟል፡

Read 1241 times