• ‹‹ስኬቴን ሳስብ በእጅጉ የሚያስደስተኝ፣ በባርሴሎና ኦሎምፒክ የወርቅ ሜዳልያ ማሸነፌ፣ ለአገራችን ሴት አትሌቶች አዲስ ምዕራፍ መክፈቱ ነው፡፡”
አትሌት ደራርቱ ቱሉ
• ‹‹ለታማሚዎቼና ለተማሪዎቼ የሚጠበቅብኝን አገልግሎት በጥሩ ሁኔታ ለመስጠትና አገሬን የተሻለች ጤናማ አገር ለማድረግ በውስጤ ቁርጠኛ አቋም አለኝ”
ዶ/ር የወይን ሃረግ ፈለቀ (ፕሮፌሰር፤ የሕክምና ዶክተር)
• ‹‹ድንቅ ተተኪ ትውልድ ለመፍጠር፣ ድንቅ ሴቶች በእናትነትም ሆነ በመሪነት ያስፈልጉናል፡፡››
ሲስተር ዘቢደር ዘውዴ (ነርስ፤ የማህበረሰብ ልማት መሪ)
• ‹‹ሁላችንም፣ እኛ ብቻ እናሳካው ዘንድ ለአንድ የተለየ ዓላማ ታስበን መፈጠራችንን ማወቅ ይገባናል፡፡ እኔ፤ ከዚህ ዓይነቱ ነፃነትን የሚያቀዳጅ ዕውቀት ብዙ ተጠቅሜያለሁ፡፡››
ዘሪቱ ከበደ (ድምጻዊት)
• ‹‹አባቴ ዩኒቨርሲቲ እንድገባ መፍቀዱን የሰሙ ሰዎች በጣም ነበር የተገረሙት:: ‹ሴትን ልጅ ወደ ዩኒቨርሲቲ ለመላክ የፈቀድከው አብደህ ነው?!› በማለት
ሀሳቡን ተቃወሙ፡፡››
ሳምያ ዘካርያ (የግብርና ስታትስቲሽያን)
• ‹‹ሴቶች ሕይወታቸውን ለማሻሻልና ህልማቸውን ለማሳካት ይችሉ ዘንድ ኀይለኛና ደፋር እንዲሆኑ እሻለሁ፡፡
ብሩታዊት ዳዊት (የኢኮኖሚ ባለሙያ)
• ‹‹እናንተም… ወንዶች የገነኑበት ሙያ ውስጥ ገብታችሁ ልትገኑበት እንደምትችሉ አትጠራጠሩ፡፡ ለምን አውሮፕላን አብራሪነት አሊያም ጠ/ሚኒስትርነት
አይሆንም? ምንም የማይቻል ነገር የለም!››
ካፒቴን አምሳለ ጓሉ (አውሮፕላን አብራሪ)
Published in
ጥበብ