Saturday, 21 December 2019 13:29

የዚምባቡዌ ም/ፕሬዚዳንት ሚስት፤ ባላቸውን በመግደል ሙከራና በማጭበርበር ተከሰሱ

Written by 
Rate this item
(1 Vote)

 የዚምባቡዌ ምክትል ፕሬዚዳንት ኮንስታንቲኖ ቺዌንጋ ባለቤት፣ ሜሪ ቺዌንጋ ባላቸውን በመግደል ሙከራና በከፍተኛ የገንዘብ ማጭበርበር ክስ እንደተመሰረተባቸው ተዘግቧል፡፡ ባለፈው ሰኞ በመዲናዋ ሃራሪ በሚገኝ ፍርድ ቤት የቀረቡት ሜሪ ቺዌንጋ፤ ባለፈው ሃምሌ ወር ደቡብ አፍሪካ ውስጥ ባለቤታቸውን ኮንስታንቲኖ ቺዌንጋን ወደ ህክምና እንዳይሄዱ በመከልከል አንዲሁም ሆስፒታል ከገቡ በኋላም የተተከለላቸውን የህክምና መሳሪያ በመንቀል ለሞት ለመዳረግ ሞክረዋል በሚል መከሰሳቸውን አልጀዚራ ዘግቧል፡፡
የ38 አመቷ ሜሪ ቺዌንጋ፣ ከዚህ በተጨማሪም፣ 1 ሚሊዮን ዶላር ያህል በማጭበርበር፣ ወደ ደቡብ አፍሪካ አሸሽተዋል በሚል የከፍተኛ ገንዘብ ማጭበርበርና የሙስና ክሶች እንደተመሰረቱባቸው የጠቆመው ዘገባው፤ ፍርድ ቤት በቅርቡ ውሳኔ ያስተላልፍባቸዋል ተብሎ እንደሚጠበቅ አመልክቷል፡፡

Read 2201 times