• ‹‹በአገሪቱ ድንቅ የጥበብ ታሪክ ውስጥ የራሴን አሻራ ማስቀመጥ በሚያስችለኝ የሙያ መስክ መሰማራት በመቻሌ፣ ራሴን እንደ ዕድለኛ ነው የምቆጥረው፡፡…››
ሳራ አበራ (ፋሽን ዲዛይነር)
• ‹‹ለአገሬ ትልልቅ ህልሞች አሉኝ:: ዴሞክራሲ እንዲሁ ለአፍ ያህል ብቻ የ ምናወራለት ሳ ይሆን ት ርጉም ያለው የሕይወታችን ዘይቤ እንዲሆን እፈልጋለሁ::››
ሶፊ ይልማ (ጋዜጠኛና ፖለቲከኛ)
• ‹‹ለስኬቴ ምስጢሩ ለሥራዬ ያለኝ ከፍተኛ ፍቅር ነው፡፡ ሥራዬ ለእኔ ሕይወቴና በጋለ ውስጣዊ ፍቅር የምተጋለት ሁሉ ነገሬም ነው፡፡››
ቆንጂት ሥነ ጊዮርጊስ (አምባሳደር)
• ‹‹ከህክምና ዶክተሮች የላቀ ገቢ የሚያገኙ የጫማ ዲዛይን ሰሪዎች፣ ከባንክ ተቆጣጣሪዎች የበለጠ የሚከፈላቸው የስፌት ሠራተኞች በሶልሬብልስ ውስጥ
መኖራቸው ያኮራኛል፡፡ ብልፅግና ይሏል ይሄ ነው!››
ቤተልሔም ጥላሁን (የሶልሬብልስ መሥራች)
• ‹‹ወደ ውስጣችሁ ተመልከቱ፤ በሕይወታችሁ ልትሰሩ ስለምትችሉት ታላቅ ነገር ራሳችሁን ጠይቁ፤ እናም አድርጉት!››
ብሩክታዊት ጥጋቡ (የሕጻናት ቴሌቪዥን ፕሮግራም ፈጣሪ)
• ‹‹እያንዳንዷን ነገር በጥልቀት እንደ መፈተሽና ውስጣዊ ባህርያቱን እንደማወቅ የሚያጓጓ ነገር የለም፡፡››
ዶ/ር ታደለች አቶምሳ (የፊዚክስ ባለሙያ፤ ተመራማሪ)
• ‹‹በኢትዮጵያ የትኛዋም ሴት ከጥቃት ነፃ አይደለችም ብዬ አምናለሁ፡፡ የፆታ ጥቃት ባይሆን እንኳን የሞራል ጥቃት አይቀርላትም፡፡››
ወንጌል ተስፋዬ (ረዳት ሳጂን፤ ወንጀል መርማሪ)
(ከ‹‹ተምሳሌት - ዕፁብ ድንቅ ኢትዮጵያውያን ሴቶች›› የተወሰደ
Published in
ጥበብ