Print this page
Saturday, 30 November 2019 12:30

በሽብርተኞች የተገደሉ ሰዎች ቁጥር መቀነሱ ተዘገበ

Written by 
Rate this item
(1 Vote)

  በአለማችን ባለፈው የፈረንጆች አመት 2018፣ ከሽብር ጥቃቶች ጋር በተያያዘ ለሞት የተዳረጉ ሰዎች ቁጥር በ15.2 በመቶ መቀነሱንና በአመቱ ለሞት የተዳረጉ ሰዎች 15 ሺህ 952 መሆናቸውን አንድ አለማቀፍ ሪፖርት አስታውቋል፡፡
ተቀማጭነቱ በሲድኒ የሆነው ኢንስቲቲዩት ፎር ኢኮኖሚክስ ኤንድ ፒስ የተባለ ተቋም ያወጣውን አመታዊ ሪፖርት ጠቅሶ ዴችዌሌ እንደዘገበው፤በሽብር ጥቃት የሞቱ ሰዎች ቁጥር ለመቀነሱ በምክንያትነት ከተጠቀሱት ጉዳዮች መካከል የአልሻባብና የአይሲስ መዳከም አንዱ ነው፡፡ በአመቱ በሽብር ጥቃት የሞቱ ሰዎች ቁጥር በከፍተኛ ሁኔታ የቀነሰባቸው ቀዳሚዎቹ የአለማችን አገራት ሶማሊያና ኢራቅ መሆናቸውንም የተቋሙ ሪፖርት ያመለክታል፡፡
በአመቱ ብዙ ሰዎችን ለሞትና ለአካል መቁሰል በመዳረግ በቀዳሚነት የተቀመጠው ቡድን የአፍጋኒስታኑ ታሊባን ሲሆን ቡድኑ 1ሺህ 443 የሽብር ጥቃቶችን በመፈጸም፣ 7 ሺህ 379 ሰዎችን ለሞት ዳርጓል ተብሏል፡፡ በ2008 በኢራቅ 1 ሺህ 131 የሽብር ጥቃቶች ተፈጽመው፣ 1 ሺህ 54 ሰዎች መገደላቸውን የጠቆመው ሪፖርቱ፤በናይጀሪያ በተፈጸሙ 562 የሽብር ጥቃቶች 2 ሺህ 40 ሰዎች መገደላቸውንም  አመልክቷል፡፡ በአመቱ ምንም እንኳን በሽብር ጥቃት ሳቢያ ለሞት የተዳረጉ ሰዎች ቁጥር ቢቀንስም፣ ሽብርተኝነት ግን በአለማቀፍ ደረጃ እየተስፋፋ መምጣቱንና በአለማችን 71 አገራት ውስጥ ቢያንስ አንድ ሰው ከሽብር ጋር በተያያዘ ለሞት መዳረጉንም ሪፖርቱ አውስቷል፡፡

Read 1130 times
Administrator

Latest from Administrator