Print this page
Saturday, 23 November 2019 12:41

በሩዋንዳ በ5 ወር የተወለዱት መንትዮች በጥሩ ጤንነት ላይ ይገኛሉ

Written by 
Rate this item
(0 votes)

  በሩዋንዳ ባለፈው ሃምሌ ወር ላይ መደበኛ የጽንሰት ጊዜያቸውን ሳይጨርሱ ባልተለመደ ሁኔታ በ5 ወራቸው የተወለዱት መንትዮች፤ በጥሩ ጤንነት ላይ እንደሚገኙ ኦል አፍሪካን ኒውስ ዘግቧል፡፡ በተረገዙ በ24 ሳምንታቸው በቅርቡ ኪጋሊ ውስጥ በሚገኘው ኪንግ ፈይሰል ሆስፒታል የተወለዱት እነዚሁ ሴትና ወንድ መንትዮች፣ ምንም እንኳን ሲወለዱ ክብደታቸው እጅግ አነስተኛ ቢሆንም፣ ያለ አንዳች የጤና ችግር እንደሚገኙ ዘገባው አመልክቷል፡፡
በተወለዱበት ጊዜ ወንዱ 660 ግራም፣ ሴቷ 620 ግራም ክብደት እንደነበራቸው ያስታወሰው ዘገባው፤ ትክክለኛው ክብደት ግን ከ2600 ግራም እስከ 4500 ግራም እንደሆነና በዚህ አነስተኛ ክብደት የተወለዱት መንትዮቹ በህይወት መቀጠላቸው እንዳስደነቃቸው የሆስፒታሉ ሃኪሞች በግርምት መናገራቸውን አመልክቷል፡፡ መንትዮቹ ያለ ጊዜያቸው ሊወለዱ የቻሉት እናታቸው ከፍተኛ የሆነ የደም ግፊት ስለተፈጠረባት መሆኑን የተናገሩት ሃኪሞቹ፤ ህጻናቱ ያለ ጊዜያቸው መወለዳቸው አስጊ በመሆኑ በልዩ ክፍል ክትትል ሲደረግላቸው እንደቆየና በአሁኑ ወቅትም በጥሩ ጤንነት ላይ እንደሚገኙ ገልጸዋል፡፡
መንትዮቹ ከተወለዱ ሶስት ወራት ያህል እንደሆናቸውና ወንዱ 2 ኪሎ ግራም ከ90 ግራም፣ ሴቷ አንድ ኪሎ ግራም ከ500 ግራም ክብደት እንዳላቸው፤ እድገታቸውም ጥሩ የሚባል እንደሆነም ዘገባው አክሎ ገልጧል፡፡

Read 2060 times
Administrator

Latest from Administrator