Print this page
Saturday, 23 November 2019 11:59

የወርቃማዋ ወፍ ምርጥ ምክሮች (ከዕውቀት ብልጭታ የተወሰደ)

Written by 
Rate this item
(7 votes)

  ከዕለታት አንድ ቀን፤ አንድ አዳኝ እጅግ ወርቃማ የሆነች አንዲት ወፍ ያጠምዳል፡፡
ወፊቱም፤
‹‹ከምታርደኝም ከምትገለኝም ሦስት ዋና ዋና ምክሮችን ልስጥህ - አለችው፡፡
‹‹እስቲ የመጀመሪያውን ልስማ›› አላት፡፡
አንደኛው፡- ‹‹የሰውን ንብረት አትመኝ››
ሁለተኛው፡- ‹‹የሰው ንብረት ተወሰደብኝ ብለህ አትቆጭ››
ሦስተኛ፡-  ‹‹ሁሉን ነገር በጊዜው ሥራው››
አለችው፡፡
የወፏን ምክር ያዳመጠው ይህ ወጣት፤ ሕይወቱ ተለወጠ፡፡
ቤት ሰራ፡፡
መኪና ገዛ፡፡
ልጅ ወለደ፡፡
የሚቀጥለው የሕይወቱ ግብ የቱ ጋ  ነው ያለው?
እሱንስ ለማትጋት ምን እናድርግ?
ዛሬም፤
‹‹ስንት እልፍ አበው ናቸው አርግዘው የሞቱ
ቀኝ እጃቸው አጥሮ ፊደል በማጣቱ
ለትምክህት አይደለም ይህን መናገሬ
ለማስቀናት እንጂ ሰነፉን ገበሬ››
***
መቀናናትማ መች ሳይቀናን ኖረ? ይህን ታሪክ ሽረን መኖር ምን ቸገረ? ብለን መጠየቅስ ማን ምን ከለከለን? ማንስ እንዳንግባባ ገራን?
‹‹በምናውቀው ስንሰቃይ የማናውቀውንም ፈርተን፣ በህሊናችንም ማቅማማት ወኔያችንንም ባህላችንም ማቅማማት ወኔያችንንም ተሰልበን
የተራመድንበት ጉልበት የመንቀሳወስ አቅሙ እያደረ ከህሊናችን ይደመሰሳል
ትርጉሙ
‹‹እፍ አንቺ መብራት ጨልሚ
ጥፊ ጨልሚ ጨልሚ
አንቺ የብርሃን ጭላንጭል
    እኔ እፍ ብዬሽ ብትወድሚ
ጭሬ ላለማሽ እችላለሁ ከቶም እንዳሻኝ ነው ስሚ››
ብሏል አቴሎ አንበሳው
ብሏል ጥቁሩ ሙር ግስላ
ማሸነፍ ነበረበትና ስሜን ደቡብ
 ደጋ ቆላ
እስከ ዛሬ አገራችን ያለባትን የአገር እዳ፤
የሚቆጣጠረው ማነው?
  ስንትስ እንደሆነ እናውቃለን ወይ? ብንጠያየቅ ምን ይመስላችኋል? ወቅቱ ዛሬ ነው! ብለን እናስብ፡፡
ዝም ብንል ብናደባ… ዘመን ስንቱን አሸንፎን
የጅልነት እኮ አይደለም፣
  እንድንቻቻል ነው
ገብቶን!
***
አገራችን የወርቃማዋ ወፍ ፍቅርና ምክር ያሻታል፡፡ ሰዓቱ አሁን ነው - መላ መላችንን እንምታ፣ አካባቢያችን እናስላ! የወደፊት መንገዳችን ይሳካ ዘንድ በየትኛውም እግር - መንገድ እንጓዝ፡፡ የቀረችን ጉዞ አጭር ናት፡፡ እንደምንም  እንጓዛት!
‹‹ማሸነፋችን በጭራሽ አጠራጣሪ አይደለም!›› ብለው የሚያምኑ አያሌ ናቸው! ኳስ ሜዳው ግን የዕምነታቸው ከቶም አጋዥ አልነበረም! ለረዥም ጊዜ ሲዳክር የቆየው የኢትዮጵያ እግር ኳስ ቡድን፤ ማንቺስተርና ሲቲን ተመልካች እንጂ የራሱን ሜዳ ወዳሽና ቀዳሽ ወይም አጣኝ መሆን አልቻለም::
ቢቀናን ሜዳችን ቢታጠን፣ ለተመልካቾቻችን ውዳሴና ሕዳሴ፣ መልክና ገጽታ መድመቂያ ይሆኑ በሆነ ነበር!
1ኛ/ የሰውን ንብረት ላለመሻት
2ኛ/ የሰው ንብረት የራስህ አልነበረምና ተወሰደብኝ ብለህ ላለመቆጨት
3ኛ/ ሁሉን ነገር በጊዜ መሥራት
እነዚህን ህግጋት ሊፈጽም ተፈጠመ!!
ሰው መሆን ያለበት ይሄንን ነው!  

Read 14310 times
Administrator

Latest from Administrator