በዚሁ ሂደት ስለ አካል ጉዳተኛ ሕፃናትና መብቶቻቸው ለሕዝቡ ለማስረዳት ጥረት ይደረጋል፡፡በትናንቱ የመክፈቻ ዝግጅት ላይ አርቲስት ቻቺ፣ ከሰበታ መርሃ እውራን ትምህርት ቤት የተወከለ አንድ አካል ጉዳተኛ ሕፃን፤ የሴቶች፣ ሕፃናትና ወጣቶች ሚኒስትር ክብርት ወይዘሮ ዘነቡ ታደሰ እና ሌሎች የክብር እንግዶች ንግግር አድርገዋል፡፡ የሲድሃርታ የሕፃናት ሙዚቃ ቡድን ጣእመ ዜማዎችን አስደምጧል፡፡ በሌላም በኩል የአፍሪካ ሕፃናት ቀንን በማስመልከት የተዘጋጀ የኪነጥበብ ዝግጅት ዛሬ እንደሚያቀርብ ዛጐል ቤተመፃህፍት ከአጋሩ ECYDO ጋር በመሆን አስታወቀ፡፡ አምስተኛው ዝግጅት ዛሬ ከጧቱ 3፡30 በሀገር ፍቅር አዳራሽ የሚቀርብ ሲሆን፤ ግጥሞች፣ ትረካዎች፣ የልጆች መዝሙሮችና ሌሎች ፕሮግራሞች ተዘጋጅተዋል፡፡