Sunday, 27 October 2019 00:00

46.8 ሚ. የአለማችን ሚሊየነሮች 158.3 ትሪሊዮን ዶላር ሃብት አፍርተዋል

Written by 
Rate this item
(1 Vote)

 የአለማችን ሚሊየነሮች ቁጥር በ2019 የፈረንጆች አመት፣ 46.8 ሚሊዮን መድረሱንና 18.61 ሚሊዮን ያህል ሚሊየነር ዜጎች የሚኖሩባት አሜሪካ፣ በሚሊየነሮች ብዛት ከአለማችን አገራት ቀዳሚነቱን መያዟን አንድ አለማቀፍ ሪፖርት አስታውቋል፡፡
ክሬዲት ሲዩሴ የተሰኘው አለማቀፍ የጥናት ተቋም ሰሞኑን ይፋ ባደረገው አመታዊው አለማቀፍ የሃብት ጥናት ሪፖርት፤የአሜሪካውያን ሚሊየነሮች ቁጥር አምና ከነበረበት የ675 ሺህ ጭማሪ በማሳየት ዘንድሮ 18.6 ሚሊዮን መድረሱንና ከአለማችን ሚሊየነሮች መካከል 40 በመቶ የሚሆኑት በአሜሪካ እንደሚገኙ አመልክቷል፡፡
4.45 ሚሊዮን ገደማ ሚሊየነሮችን ያፈራችው ቻይና፣ በሚሊየነሮች ብዛት ከአለማችን አገራት የሁለተኛነት ደረጃን መያዟን የጠቆመውና ተቋሙ ለ10ኛ ጊዜ ይፋ ያደረገው ሪፖርቱ፤ ጃፓን በ3.03 ሚሊዮን ያህል ሚሊየነሮች የሶስተኛ ደረጃን መያዟን አስታውቋል፡፡
በመላው አለም የሚገኙት 46.8 ሚሊዮን ያህል ሚሊየነሮች በድምሩ 158.3 ትሪሊዮን ዶላር ገደማ ሃብት ማፍራታቸውን የገለጸው ሪፖርቱ፤ይህም ከአለማችን አጠቃላይ ሃብት ግማሽ ያህሉን እንደሚይዝ አመልክቷል፡፡

Read 2698 times