Print this page
Saturday, 31 August 2019 13:39

የቀድሞው የማሌዢያ ጠ/ሚ በግዙፍ የሙስና ቅሌት ተከሰዋል

Written by 
Rate this item
(1 Vote)

   ኡጋንዳዊው ተማሪ ብሎክ አድርገውኛል በሚል ፕሬዚዳንቱን ከሷቸዋል

           የቀድሞው የማሌዢያ ጠቅላይ ሚኒስትር ናጂብ ራዛቅ፣ ከ4.5 ቢሊዮን ዶላር በላይ የህዝብ ገንዘብ በሙስና በመመዝበር ለግል ጥቅማቸው አውለዋል በሚል በተመሰረተባቸውና በአለማችን ግዙፉ የሙስና ቅሌት እንደሆነ በተነገረለት የሙስና ክስ ፍርድ ቤት ቀርበዋል፡፡
ናጂብ ራዛቅ በስልጣን ዘመናቸው የመዘበሩትን የህዝብ ገንዘብ እጅግ ዘመናዊ የአሜሪካ የቅንጦት ቤቶችን ከመግዛት አንስቶ ራሳቸውንና ቤተሰባቸውን ከሚገባው በላይ ለማቀናጣት ተጠቅመውበታል መባሉን የዘገበው ዘ ጋርዲያን፤በአጠቃላይ 25 ክሶች እንደተመሰረቱባቸውና ሁሉንም ክሶች ክደው እንደተከራከሩ አመልክቷል፡፡
በሌላ በኩል ደግሞ በቫርቫርድ ዩኒቨርሲቲ የሁለተኛ ዲግሪ ትምህርቱን በመከታተል ላይ የሚገኘው ኡጋንዳዊው ወጣት ቴለር ሴጉያ፣ በትዊተር ገጹ ላይ አምባገነን ብሎ ስለጠራቸው ብቻ ብሎክ ያደረጉትን የአገሪቱን ፕሬዚዳንት ዮሪ ሙሴቬኒን በፍርድ ቤት መክሰሱ ተዘግቧል፡፡
ወጣቱ በሙሴቬኒ ላይ በመሰረተው ክስ፣ ሀሳቤን በነጻነት የመግለጽና የመወያየት መብቴን ጥሰዋልና ቅጣት ይገባቸዋል ማለቱን የጠቆመው ዘገባው፤ በመዲናዋ ካምፓላ የሚገኘው ፍርድ ቤት ጉዳዩን እየመረመረው እንደሚገኝም አመልክቷል፡፡

Read 1335 times
Administrator

Latest from Administrator