የደቡብ ሱዳን ፕሬዚዳንት ሳልቫ ኬር፤ እሳቸው በሌሉበት የአገሪቱ ብሔራዊ መዝሙር እንዳይዘመር የሚከለክል ህግ ማውጣታቸውን የአገሪቱን የማስታወቂያ ሚኒስትር ጠቅሶ አጃንስ ፍራንስ ፕሬስ ዘግቧል፡፡
የአገሪቱ የሕዝብ መዝሙር ከኤምባሲዎችና ከትምህርት ቤቶች በስተቀር በሌሎች ቦታዎች መዘመር የሚችለው ፕሬዚዳንት ሳልቫ ኬር በስፍራው ከተገኙ ብቻ እንዲሆን ፕሬዚዳንቱ ባለፈው አርብ ባደረጉት የካቢኔ ስብሰባ ውሳኔ ማስተላለፋቸውን ማስታወቂያ ሚኒስትሩ ማይክል ማኩዌል በይፋ ማስታወቃቸውን ዘገባው አመልክቷል፡፡
የተለያዩ ባለስልጣናትና ተቋማት የህዝብ መዝሙሩን ዜማና ግጥም በቅጡ ሳይለማመዱ እንደነገሩ ሲዘምሩት እንደሚታዩ የጠቆሙት ሚኒስትሩ፤ “ይህም የአገሪቱን ብሄራዊ ክብር የሚነካ ነው፣ ብሄራዊ መዝሙር ፕሬዚዳንቱ በተገኙበት ብቻ የሚዘመር እንጂ ማንም ተራ ዜጋ የሚያበላሸው አይደለም” ብለዋል፡፡
የሳልቫ ኬር መንግስት ፕሬዚዳንቱ በሌሉበት የህዝብ መዝሙር እንዳይዘመር ቢከለክልም፤ ድርጊቱን በፈጸሙ ላይ የሚወሰደውን እርምጃ በተመለከተ ግን ሚኒስትሩ ያሉት ነገር እንደሌለ ዘገባው ገልጧል፡፡
Published in
ከአለም ዙሪያ
Latest from Administrator
- የእስራኤል እና የኢራን ፍጥጫ
- Insights on Israel's Response: Interview with Mr. Tomer Bar-Lavi, Chargé d’Affaires at the Embassy of Israel to Ethiopia
- Barr, a vocal Trump critic, says he will ‘support the Republican ticket’ in November
- Iran president warns of ‘massive’ response if Israel launches ‘tiniest invasion’
- "አልሞቷል" ፊልም ዛሬ በዓለም ሲኒማ ይመረቃል