የሰሜን ኮርያው ፕሬዚዳንት ኪም ጁንግ ኡን፣ ከታዋቂው የአገሪቱ የውትድርና ዩኒቨርሲቲ በማዕረግ መመረቃቸው መዘገቡን ተከትሎ ፕሬዚዳንቱ አንድም ቀን ትምህርታቸውን በቅጡ ተከታትለው እንደማያውቁ እርግጠኞች ነን የሚሉ ውስጥ አዋቂዎች ጉዳዩን መሳለቂያ እንዳደረጉት ቢዝነስ ኢንሳይደር ዘግቧል፡፡
ኪም ጁንግ ኡን በአያታቸው ስም ከተሰየመው ታላቁ የኪም ኢ ሱንግ የውትድርና ዩኒቨርሲቲ በማዕረግ መመረቃቸውን የመንግስት መገናኛ ብዙሃን በስፋት መዘገባቸውን የጠቆመው ቢዝነስ ኢንሳይደር፤ አንዳንድ ውስጥ አዋቂዎች ግን “ወደ ዩኒቨርሲቲው ግቢ ድርሽ ብሎ አያውቅም፤ እንደለመደው ዝና ፍለጋ ያስወራው ወሬ ነው” በማለት ፕሬዚዳንቱን መተቸታቸውን አመልክቷል፡፡
ፕሬዚዳንቱ በዩኒቨርሲቲው ውስጥ መማራቸውን የሚያሳይ ምንም አይነት የፎቶግራፍ፣ የጽሁፍም ሆነ የሰነድ ማስረጃ እንደሌለ የተናገሩት አንድ የአገሪቱ የቀድሞ የጦር ሃይል አባል፤ “እንኳን በማዕረግ ሊመረቁ ዩኒቨርሲቲው ግቢ ውስጥ ገብተው አያውቁም” ሲሉ የምርቃት ዜናውን ማጣጣላቸውን ዘገባው ገልጧል፡፡
Published in
ከአለም ዙሪያ
Latest from Administrator
- የእስራኤል እና የኢራን ፍጥጫ
- Insights on Israel's Response: Interview with Mr. Tomer Bar-Lavi, Chargé d’Affaires at the Embassy of Israel to Ethiopia
- Barr, a vocal Trump critic, says he will ‘support the Republican ticket’ in November
- Iran president warns of ‘massive’ response if Israel launches ‘tiniest invasion’
- "አልሞቷል" ፊልም ዛሬ በዓለም ሲኒማ ይመረቃል