Tuesday, 02 July 2019 12:20

በአየር ብክለት ሳቢያ በየ1 ሰዓቱ 800 ሰዎች ለሞት ይዳረጋሉ

Written by 
Rate this item
(1 Vote)


      በመላው አለም ከአየር ብክለት ጋር በተያያዘ በሚከሰቱ የካንሰርና የመተንፈሻ አካላት በሽታዎች በየአመቱ 7 ሚሊዮን ያህል ሰዎች ወይም በየአንድ ሰዓቱ 800 ያህል ሰዎች ለሞት እንደሚዳረጉ የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ባወጣው አመታዊ ሪፖርት አስታውቋል፡፡
በአለማችን ከ6 ሚሊዮን በላይ የሚሆኑ የተለያዩ አገራት ዜጎች ጤናቸውን አደጋ ላይ የሚጥል የተበከለ አየር እንደሚተነፍሱ የጠቆመው ተመድ፣ ከሰላሳ በመቶ በላይ ያህሉም ህጻናት መሆናቸውን ባለፈው ሳምንት ባወጣው አለማቀፍ ሪፖርት አመልክቷል፡፡
ከአለማችን ህዝብ 90 በመቶው ለአየር ብክለት የተጋለጠ እንደሆነ ያመለከተው ሪፖርቱ፣ 93 በመቶ የአለማችን ህጻናት የአለም የጤና ድርጅት ካስቀመጠው የአየር ብክለት ደረጃ በከፋ ሁኔታ ውስጥ እንደሚኖሩና በየአመቱ 600 ሺህ ያህል ህጻናት በአየር ብክለት ሳቢያ ካለጊዜያቸው እንደሚሞቱም ገልጧል፡፡
በመላው አለም በየአመቱ ከአየር ብክለት ጋር በተያያዘ ለሞት የሚዳረጉ ሰዎች ቁጥር በወባ፣ በሳንባ ነቀርሳና በኤች አይ ቪ ኤድስ ሳቢያ ከሚሞቱት አጠቃላይ ሰዎች ቁጥር በሶስት እጥፍ ያህል እንደሚበልጥም ሪፖርቱ አመልክቷል፡፡


Read 4513 times