Tuesday, 02 July 2019 12:16

ሆንግ ኮንግ ዘንድሮም በኑሮ ውድነት ቀዳሚዋ ከተማ ሆናለች

Written by 
Rate this item
(0 votes)

 አዲስ አበባ ከ209 የአለማችን ከተሞች 171ኛ ደረጃን ይዛለች

     ባለፈው አመት ከአለማችን ከተሞች ለኑሮ እጅግ ውድ በመሆን ቀዳሚነቱን ይዛ የነበረችው ሆንግ ኮንግ ዘንድሮም በአንደኛ ደረጃ ላይ መቀመጧን የዘገበው ዘ ኢንዲፔንደንት፤ መዲናችን አዲስ አበባ ከአለማችን 209 ከተሞች በኑሮ ውድነት 171ኛ ደረጃን መያዟን አመልክቷል፡፡
ሜርሰር የተሰኘው አለማቀፍ የጥናት ተቋም፤ በአለማችን 209 ከተሞች ላይ ያደረገውን የኑሮ ውድነት ጥናት መሰረት አድርጎ ሰሞኑን ያወጣውን አመታዊ ሪፖርት ጠቅሶ ዘገባው እንዳለው፣ ቶክዮ ለኑሮ ውድ በመሆን የ2ኛ ደረጃን ስትይዝ ሲንጋፖር በ3ኛነት ትከተላለች፡፡
ተቋሙ በከተሞች ያለውን የቤት፣ የትራንስፖርት፣ የምግብና የአልባሳትን ጨምሮ የተለያዩ 200 ያህል ሸቀጦችንና አገልግሎቶችን ዋጋ በማጥናት ከአንደኛ እስከ አስረኛ ደረጃ ካስቀመጣቸው አገራት መካከል ስምንቱ በእስያ እንደሚገኙም ዘገባው አመልክቷል፡፡
ሴኡል፣ ዙሪክ፣ ሻንጋይ፣ አሽጋባት፣ ቤጂንግ፣ ኒውዮርክና ሻንዜን እንደ ቅደም ተከተላቸው ከአራተኛ እስከ አስረኛ ያለውን ደረጃ የያዙ የአመቱ የአለማችን ውድ ከተሞች መሆናቸው ተነግሯል፡፡ ለኑሮ እጅግ እርካሽ በሚል ከአለማችን አገራት መካከል በአንደኛነት የተቀመጠችው የቱኒዚያ መዲና ቱኒዝ ስትሆን፣ የኡዝቤክስታኗ ታሽኬንት በ2ኛ፣ የፓኪስታን ርዕሰ መዲና ካራቺ ደግሞ በ3ኛ ደረጃ ላይ ተቀምጠዋል፡፡

Read 1335 times