Saturday, 02 June 2012 10:36

“ሜን ኢን ብላክ 3” ከቀድሞዎቹ በገቢ የተሻለ ሆኗል

Written by  ግሩም ሠይፉ
Rate this item
(0 votes)

ሰሞኑን ለዕይታ የበቃው “ሜን ኢን ብላክ 3” በ203.2 ሚሊዮን ዶላር ሳምንታዊ ገቢ ቦክስ ኦፊስን እየመራ ነው፡፡ በ230 ሚሊዮን ዶላር በጀት የተሰራው  ፊልሙ፤ቀደም ብለው ከተሰሩት  ሁለት ክፍሎቹ እጥፍ ገቢ ማስገኘቱ ሲታወቅ፤ የፊልሙን ክፍል 4 ለመስራት እንዳነሳሳም እየተነገረ ነው፡፡ በሰሜን አሜሪካ ባለፈው ሳምንት ለእይታ የበቃው ፊልሙ፤በአራት ቀናት ውስጥ 70 ሚሊዮን ዶላር አስገኝቶዋል፡፡ በሌሎች የዓለም ክፍሎች ደግሞ 133.2 ሚሊዮን ዶላር በማስገባት ጠቅላላ ገቢው 203.2 ሚሊዮን ዶላር ሊደርስ ችሏል፡፡

“ሜን ኢን ብላክ 3” የተሰራው በሶኒ ፒክቸርስ ሲሆን የፊልም ኩባንያው በሚቀጥሉት ሁለት ወራት ሌሎች ትላልቅ ፊልሞችን ለገበያ በማብቃት ገበያውን የመቆጣጠር እቅድ እንዳለው ሮይተርስ አመልክቷል፡፡ “ሜን ኢን ብላክ 3” እንዲሁም በድጋሚ የተሰሩት “ዘ አሜዚንግ ስፓይደር ማን” እና “ቶታል ሪኮል” ፊልሞችን ለማስተዋወቅ 1ቢሊዮን ዶላር ወጪ መደረጉ ተዘግቡዋል፡፡

በሶኒ ፒክቸርስ በ215 ሚሊዮን ዶላር በጀት በድጋሚ የተሰራው “ዘ አሜዚንግ ስፓይደር ማን” ለወጪ ቅነሳ ሲባል አዲስ ተዋናይ እንዲሰራው መደረጉን የገለፀው ሮይተርስ፤ ከ12 ዓመታት በፊት በሸዋዚንገር ተተውኖ የነበረው “ቶታል ሪኮል”  በኮሊን ፋሬል እንደተሰራና 125 ሚሊዮን ዶላር ወጭ እንደተደረገበት አውስቷል፡፡

 

 

Read 1045 times Last modified on Saturday, 02 June 2012 10:42