Sunday, 12 May 2019 00:00

በጀርመን ከ6 ሚ. በላይ ሰዎች ማንበብና መጻፍ አይችሉም

Written by 
Rate this item
(0 votes)

 90 በመቶ የጋና የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ፈተና አላለፉም

              በአገረ ጀርመን ከ6 ሚሊዮን በላይ የሚሆኑ ሰዎች በአገሪቱ ብሄራዊ ቋንቋ ማንበብና መጻፍ እንደማይችሉ ዴች ዌሌ ዘግቧል፡፡
ባለፈው ማክሰኞ ይፋ የተደረገውን አገር አቀፍ የትምህርት ሁኔታ ጥናት ጠቅሶ ዘገባው እንዳለው፣ በአገሪቱ የሚኖሩ 6.2 ሚሊዮን ሰዎች ጀርመንኛን በአግባቡ ማንበብና መጻፍ እንደማይችሉ፣ አንድ አረፍተ ነገር ለመመስረት በእጅጉ እንደሚቸገሩ ለማረጋገጥ ተችሏል፡፡ በጀርመንኛ ቋንቋ ማንበብና መጻፍ ከማይችሉት ከእነዚህ ሰዎች መካከል 47.4 በመቶ የሚሆኑት ስደተኞችና የሌሎች አገራት ዜጎች መሆናቸውን የጠቆመው ዘገባው፤ በጀርመንኛ አፋቸውን ከፈቱት መካከልም 7.3 በመቶ ያህሉ የማንበብና የመጻፍ ችግር እንዳለባቸው አመልክቷል፡፡
በተያያዘ ዜና ደግሞ፣ በጋና የዩኒቨርሲቲ የሚማሩ 90 በመቶ የህግ ተማሪዎች በፈተና መውደቃቸው አነጋጋሪ ሆኖ መሰንበቱን ቢቢሲ ዘግቧል፡፡ የአገሪቱ የከፍተኛ ትምህርት ፈተና ኮሚቴ ያወጣውን መረጃ ጠቅሶ ዘገባው እንዳለው፤ ይህን ያህል መጠን ያለው ተማሪ መውደቁ ያበሳጫቸው አንዳንድ የዩኒቨርሲቲ መምህራን ስራቸውን ለማቋረጥ እንደወሰኑ ማስታወቃቸውን አመልክቷል፡፡

Read 1079 times