የጐንደር ከተማ የዓለም የቤተመዘክር ቀንን ለመጀመሪያ ጊዜ አከበረች፡፡ በዓለም ለ35ኛ በኢትዮጵያ ደግሞ ለአስረኛ ጊዜ የተከበረውን ቀን ከተማዋ ያከበረችው የቤተመዘክር ፋይዳ ላይ በተደረገ የፓናል ውይይት እና የሽልማት ሥነ ሥርዓት እንደሆነ ታውቋል፡፡ ትናንት በሥነጽሑፍ ውድድር አሸናፊ ሆነው የተመረጡ ፀሐፍት ሽልማታቸውን ተቀብለዋል፡፡ ጐንደር አንድ መንግስታዊና አምስት የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስትያን ንብረት የሆኑ አብያተ መዘክር አሏት፡፡