በዶ/ር ቸርነት ገ/ክርስቶስ የተፃፈውና ሀኪምንና ህክምናን ማህበረ ፖለቲካንና ሳይንስን ያጣመረው “ዲባቶ” የተሰኘ ልብ ወለድ መፅሐፉ ዛሬ ሳር ቤት አካባቢ በሚገኘው ኪንግስ ሆቴል ከቀኑ 9፡00 ጀምሮ እንደሚመረቅ የምርቃቱ አዘጋጅ ሰምና ወርቅ ሚዲያና ኢንተርቴይንመንት አስታወቀ፡፡በሥነስርዓቱ ላይ በመፅሐፉ ላይ ውይይት የሚደረግ ሲሆን የተለያዩ ኪነ ጥበባዊ ዝግጅቶችም ይቀርባሉ ተብሏል፡፡ በ371 ገፆች የተቀነበበው መፅሐፉ፤ በ160 ብርና በ20 ዶላር ይሸጣል፡፡