ከአራት ወራት በፊት ከአሜሪካው አቻቸው ዶናልድ ትራምፕ ጋር ታሪካዊ የተባለውን ስብሰባ በማድረግ ከአለም ጋር የነበራቸውን ለአመታት የዘለቀ ኩርፊያ የደመሰሱት የሰሜን ኮርያው ፕሬዚዳንት ኪም ጆንግ ኡን፣ በቅርቡም አገራቸው የተጣሉባት ማዕቀቦች እንዲነሱላት ለማግባባት በማሰብ ከ5 የአለማችን አገራት መሪዎች ጋር ተገናኝተው ለመምከር ማቀዳቸውን ብሉምበርግ ዘግቧል፡፡
ኪም ጁንግ ኡን ከደቡብ ኮርያው ፕሬዚዳንት ሙን ጃኢን እና ከቻይናው ፕሬዚዳንት ዢ ጂፒንግ ጋር በአጭር ጊዜ ውስጥ ተገናኝተው እንደሚወያዩ መነገሩን የጠቆመው ዘገባው፣ ከጥቂት ወራት በኋላም ከጃፓኑን ፕሬዚዳንት ሺንዙ አቤ ጋር ይገናኛሉ ተብሎ እንደሚጠበቅ አመልክቷል፡፡
ከአሜሪካው አቻቸው ዶናልድ ትራምፕ ጋር በመጪው ወር በድጋሚ ለመገናኘት ሳያስቡ አልቀሩም የተባሉት የወትሮው አመጸኛ ኪም ጁንግ ኡን፣ በዚያው ሰሞን ወደ ሩስያ አቅንተው ከፕሬዚዳንት ቭላድሚር ፑቲን ጋር ስብሰባ ያደርጋሉ ተብሎ እንደሚጠበቅና “ይምጡና እንማከር” ብለው ለሮማው ሊቀ ጳጳስ ፍራንሲስ የክብር ግብዣ መላካቸውንም ዘገባው ገልጧል፡፡
Published in
ከአለም ዙሪያ