ባለፈው እሑድ በዋናው የግማሽ ማራቶን ውድድር ላለፉት ሁለት ዓመታት አሸናፊ የነበሩት ኬንያውያን አልተሳካላቸውም፡፡ኢትዮጵያውያንና ኬንያውያን ታዋቂ አትሌቶች በተሳተፉበት የሴቶች 21 ኪሎ ሜትር የማረሚያ ቤቶቿ አትሌት ዘይቱና አረዋ ርቀቱን 1 ሰዓት 13 ደቂቃ 40 ሰከንድ አጠናቃ ስታሸንፍ፣ ሁለተኛ የማረሚያ ቤቶቿ ጽጌረዳ ግርማ ሦስተኛ ቀነኔ ሆነዋል፡፡ በወንዶች ምድብ የግል ተወዳዳሪው ሀብታሙ አሰፋ 1 ሰዓት 03 ደቂቃ፣ 38 ሰከንድ በማጠናቀቅ አንደኛ ሲወጣ፣ ስንታየሁ መርጋና ፀጋዬ አሰፋ ከኦሮሚያ ፖሊስና በግል ሁለተኛና ሦስተኛ ሆነው የብርና ነሐስ ተሸላሚ ሆነዋል፡፡ በሁለቱም ጾታ ከአንደኛ እስከ ሦስተኛ በመውጣት ያጠናቀቁ አትሌቶች የአሥራ አራት፣ የሰባት እና የሦስት ሺሕ ብር የገንዘብ ሽልማት ተበርክቶላቸዋል፡፡
በሌላ በኩል በታዋቂ አትሌቶች መካከል በተደረገው ሰባት ኪሎ ሜትር የሩጫ ውድድር ሴቶች፣ ፀጋ ደሳለኝ ቀዳሚ ሆና ስታጠናቅቅ ሁለተኛና ሦስተኛ የወጡት ደግሞ ትዕግስት ተካና ሃና አሕመድ ናቸው፡፡ በተመሳሳይ ርቀት ወንዶች የሻሸመኔ አትሌቲክስ ክለብን ወክሎ የተወዳደረው መርዕድ መኮንን አንደኛ ሲወጣ፣ የደቡብ ፖሊሶቹ ደጀኔ ሙላይ እና አብዱሶ ማላ ሁለተኛና የመጀመሪያ ማራቶንን ለማካሄድ የታላቁ ሩጫ በኢትዮጵያ ላይ እየተሯሯጠ ነው፡፡ በሌላ በኩል ቀዋል፡፡ ብዙኀን የተሳተፉበት የሰባት ኪሎ ሜትርና ሁለት ኪሎ ሜትር የሸፈነ የሕፃናት ውድድር ተካሒዷል፡፡በአጠቃላይ ታዋቂ አትሌቶቹን ጨምሮ በዚህ ‹‹ሁሉም›› ዘመቻ ቁጥራቸው እስከ አሥር ሺሕ የሚገመቱ ተወዳዳሪዎች ነበሩ፡፡ በክብር እንግድነት ኃይሌ ገብረ ሥላሴን ጨምሮ የተለያዩ መንግሥታዊና መንግሥታዊ ካልሆኑ ድርጅቶች ኃላፊዎች ተገኝተዋል፡፡ በተመጣጠነ ምግብ ምክንያት የእናቶችና ሕፃናት ሞትን በመከላከል ላይ ትኩረት ያደረጉ መርሆች በውድድሮቹ ታጅበው ቀርበዋል፡፡