Saturday, 22 September 2018 14:41

‹‹…ማህበረሰቡን …ለማገልገል ዝግጁ ነን…››

Written by 
Rate this item
(0 votes)

 የኢትዮጵያ የጽንስና ማህጸን ሀኪሞች ማህበር በአሜሪካ ከሚገኘው የአሜሪካን የጽንስና ማህጸን ሐኪሞች ኮሌጅ ጋር በመተባበር የተለያዩ ፕሮጀክቶችን ቀርጾ ደጋፍ በሚያደርጉ ድርጅቶች አጋዥነት ስራ ከጀመረ እነሆ ሁለት አመታት ተቆጥረዋል፡፡ በእነዚህ ሁለት አመታት ጊዜ ውስጥ የተሰሩ ስራዎችን በሚመለከት አንዳንዶቹን እንደሚከተለው ለንባብ ብለናል፡፡
RESIDENCY: -
ከጠቅላላ ሐኪምነት ወደ ጽንስና ማህጸን ሕክምና እስፔሻሊስትነት የሚሰለጥኑ ባለሙያዎች በአገር አቀፍ ደረጃ በተመሳሳይ የትምርት መመሪያ እንዲሰለጥኑና ብቃት እና ጥራት ባለው መንገድ ለህብረተሰቡ አገልግሎት እንዲሰጡ የሚያስችል ስራ ከጤና ጥበቃ እና ከትምህርት ሚኒስቴር ጋር በመሆን በጋራ ስራ ተሰርቶአል፡፡ ለሚማሩ ሰዎች ጥሩ ትምህርት መስጠት፤ ጥሩ ጥናትና ምርምር ማድረግ ፤የተሻለና ጥሩ የሆነ ሕክምና መስጠት የሚሉትን ነጥቦች ተግባራዊ ማድረግ የሚያስፈልግበት ምክንያትም የድህረ ምረቃ ትምህርቶቹ ከበሽተኛ ጋር የተገናኙ በመሆናቸውና ሐኪሙ ብዙ እናቶችን በሕክምናው አገልግሎት የመርዳት ኃላፊነት ስለአለበት በጥሩ ሁኔታ መሰራት እንዳለበት ስለታመነ ነው፡፡
ETHICS: -  
ሌላው የፕሮጀክቱ ዘርፍ የጽንስና ማህጸን ህክምና ባለሙያዎች የስነምግባር መመሪያን መቅረጽ ነው፡፡ የማህጸን እና ጽንስ ሐኪሞች ለሕመምተኛው መደረግ ያለበት የትኛው ነው ?የሚለውን ለመወሰን የሕመም ተኛው ፈቃድ፤ የሚኖረው አቅም የመሳሰሉት ሁሉ የሚያስፈልጉ ሲሆን ይህንን በትክክ ለኛው መን ገድ ለመምራት የሚያስችል የስነ ምግባር መመሪያ  በመዘጋጀት ላይ ነው ፡፡
CME: -
የህክምና ባለሙያዎች በስራ ላይ ባሉባቸው ጊዜያት እውቀታቸውን ከተለያዩ ሳይንሳዊ ግኝቶች እና አሰራሮች አንጻር የሚፈትሹባቸው ቀጣይነት ያለው ስልጠና እንዲያገኙ ማገዝ አንዱ  የESOG_ACOG ፕሮጀክት አቅጣጫ ነው፡፡ የጽንስና ማህጸን ሐኪሞች በዚህ ዘርፍ ጊዜው በሚፈቅደው የአገልግሎት አሰጣጥ ውስጥ እንዲያልፉ የሚያስችል አሰራር ነው፡፡
LEADERSHIP: -
የአመራር ብቃትን ማጎልበት ለጽንስና ማህጸን ሐኪሙ እጅግ ጠቃሚ በመሆኑና በስራ ላይ ያሉ ጉድለቶችን ለማስተካከል የሚረዳ በመሆኑ ባለሙያዎቹ በተወሰኑ ጊዜያት ስልጠና እንዲወስዱ እየተደረገ ነው፡፡ Transformational leadership በሚል የማህጸንና ጽንስ ሕክምና ባለ ሙያዎች መሰልጠናቸው በተለይም በተለያዩ ዩኒቨርሲቲዎች ውስጥ የማህጸንና ጽንስ ሕክምና ሙያን በማስተማር ላይ ለሚገኙት እጅግ ጠቃሚ ነው፡፡
ከተጠቀሱት በተጨማሪ የኢትዮጵያ የጽንስና ማህጸን ሐኪሞች ማህበር ቀደም ብሎ የጀመራ ቸውን ሳይንሳዊ ምርም ሮችን የሚያሳትምበት ጆርናልና ፤በተለያዩ የመገናኛ ብዙሀን ለህብረ ተሰቡ ስለጤንነቱ እንዲያ ውቅና አስቀድሞ እራሱን እንዲከላከል የሚያስችል ስራ የሚሰራባ ቸውን የመገናኛ ብዙሀን ስራዎች ማሳደግና የተሻለ ጥራት እንዲኖራቸው እገዛ ከማድረግ ባሻገር ሐኪሞች ባሉበት ቦታ ሆነው በኢንተርኔት አማካኝነት ትምህርትና መረጃዎችን እንዲያገኙ የማድረግ እና ሌሎችንም ተያያዥነት ያላቸውን ስራዎችን በመተግበር ላይ ነው፡፡
የኢትዮጵያ የጽንስና ማህጸን ሐኪሞች ማህበር ከሚቺጋን ዩኒቨርሲቲ (CIRHT) The Central For International Reproductive Health Training Of The University of Michigan ) በሚገኝ የገንዘብ ድጋፍ ለአምስት አመት ሊተገብረው የታሰበው ፕሮጀክት በሁለት አመቱ ወደ ኢትዮጵያ ፌደራላዊ ዲሞክራሲያው ጤና ጥበቃ ሚኒስቴር እንዲዛወር የመደረጉን ምክንያት ፕሮጀክቱ ስራውን ሲጀምር የኢሶግ ቦርድ ፕሬዝዳንት የነበሩት የማህጸንና ጽንስ ሕክምና እስፔሻሊስት  የሆኑት ዶ/ር ደረጀ ንጉሴ ለዚህ እትም አብራርተዋል፡፡
ዶ/ር ደረጀ እንደገለጹት ‹‹… ከአሜሪካ የማህጸንና ጽንስ ሐኪሞች ማህበር  ጋር የተጀመረው ፕሮጀክት ጽንሰ ሐሳብ ኢሶግ  ከነበሩት ስትራቴጂክ ዶክመንቶች ውስጥ አንዱ በተለይም እንደውጭው አቆጣጠር ከ2012-2016/ የነበረውን የአምስት አመት ተግባራት በሚያመላክተው ውስጥ ማህበሩ በዚህ ፕሮጀክት ስንፈጽማቸው የነበሩትን ተግባራት እና ሌሎችንም ማህበሩ ከነበረው ራእይና ተልእኮ ጋር የተያያዘ ስለሆነ ይህንን ተግባር ዋነኛ ማድረግ ይገባል የሚል እቅድ ነበረ፡፡ስለዚህም እኔ የቦርድ ፕሬዝዳንት ሆኜ ስመረጥ ከ2014/እንደውጭው አቆጣጠር ጀምሮ ዶክመንቱን በመፈተሸ ከላይ የተዘረዘሩትን ተግባራት ለመምራት የሚያስችለን የኢትዮ ጵያ የማህጸንና ጽንስ ሕክምና ኮሌጅ መመስረት ያስፈልጋል የሚል እምነት አደረብን፡፡ ስለዚ ህም ሶስት ልምድ ያላቸው ሐኪሞች ተመድበው ስራውን እንዲከታተሉ ሲደረግ እኔም ነበርኩ በት፡፡ ይህንን ጉዳይ በስራ ከምናገኛቸው የተለያዩ የማህጸንና ጽንስ ሕክምና ባለሙያዎች  ጋር በመመካከር ስራው ከአሜሪካ የማህጸንና ጽንስ ኮሌጅ ጋር የምንሰራበት መንገድ ስለተመቻቸ June/ 2016/  የመግባቢያ ሰነዱ ተፈርሞአል፡፡
ዶ/ር ደረጀ ንጉሴ አስከትለው እንደተናገሩትም በኢሶግ ስትራቴጂክ ዶክመንት ላይ የተገለጸው በውጭው አቆጣጠር በ2020/ የኢትዮጵያ የማህጸንና ጽንስ ኮሌጅ እንደሚመሰረት ነው፡፡ የተጀ መሩት ስራዎች በአምስት አመት ጊዜ ውስጥ ሲያልቁ እራሱን የቻለ ኮሌጅ ተመዝግቦ ስራ ይጀምራል የሚል እቅድ ተነድፎ ነበር፡፡ ነገር ግን ከድጋፍ አድራጊዎች ወገን ባልታሰበ ሁኔታ የሚገኘው እገዛ በውጭው አቆጣጠር ከሴፕቴምር 30/2018/በሁዋላ እንደማይቀጥል ስለተነገረን ይህ ዱብእዳ እንደሚባለው አስደንጋጭ ዜና ነበር፡፡ ይህ ሁኔታ በአለምአቀፍ ደረጃ ካለው ድጋፍ የማድረግ እንዲሁም የገንዘብ አሰጣጥ ፍሰትና በተወሰነ መልኩም የጤና ጥበቃ ሚኒስቴርም ከአሁን በሁዋላ ስራውን እየመራ መቀጠል ይችላል ከሚል እምነት ጋር የተያያዘ ነው፡፡ ስለ ዚህም የአሜሪካው የማህጸንና ጽንስ ኮሌጅ የሚያገኘው የገንዘብ ድጋፍ ስለሚቋረጥ በቀጣይነት ከኢሶግ ጋር ለመስራት ምቹ ሁኔታ አለመኖሩን ተነግሮን ፕሮጀክቱ እንዲቋረጥ ተገድዶአል፡፡›› ብለዋል፡፡
የተጀመሩት ስራዎችን ቀጣይነት በሚመለከት ዶ/ር ደረጀ እንዳሉት‹‹…ኢሶግ ላለፉት 27/ አመ ታት በኢትዮጵያ የስነተዋልዶ ጤና ላይ ብዙ ሰርቶአል፡፡ በዚህም የተነሳ በተለያዩ የስነተ ዋልዶ ጤና ዙሪያ ከተለያዩ ድጋፍ አድራጊዎች ጋር የሰራ በመሆኑ ጥሩ አጋር መሆኑን ማሳ የት የቻለ ማህበር ነው፡፡ ስለዚህም አሁን የተጀመሩትን በጎ ስራዎች ከሌሎች አጋር ድርጅቶች ጋር በመሆን መቀጠል ይቻላል፡፡ አሁን ፕሮጀክቱ ተቋርጦአል ቢባልም ለተወሰኑ ወራት ድጋፉ እንደሚቀጥል ቃል የገቡ በመሆኑ ለወደፊትም ከእነሱው ጋር ይቀጥል ወይንም ስራውን እየሰራን ሌሎች ድጋፍ አድራጊዎችን ማፈላለግ ያስፈልጋል የሚለውን የምናየው ይሆናል፡፡ ዶ/ር ደረጀ ንጉሴ በስተመጨረሻው እንደገለጹት በኢትዮጵያ የህክምና ታሪክ በተለይም ሙያውን በልዩ ደረጃ በማሰልጠን ረገድ የኢትዮጵያ የማህጸንና ጽንስ ሕክምና ማህበር ባለፉት ሁለት አመታት በተደረገለት የገንዘብም ሆነ የሙያ ድጋፍ የሰራው ስራ የመጀመሪያ ነው፡፡  
ኢትዮጵያ ውስጥ የማህጸንና ጽንስ ሕክምና ትምህርትን የሚሰጡ ተቋማት በሙሉ አንድ አይነት የሆነ የትምህርት መርሐ ግብር እንዲኖራቸው ለማስቻል ከጤና ጥበቃ እና ከትምህርት ሚኒስቴር ጋር በመሆን ስራ ተሰርቶአል፡፡ ደረጃውን የጠበቀ ፈተናን መስጠትን በተመለከተም ተሳክቶ ተካሂዶአል፡፡ ጥራቱን የጠበቀ ተከታታይ የህክምና ትምህርት መስጠትን በተመለከተም ባለሙያዎችን ለልዩ ሙያ በማሰልጠን ረገድ ካሉ ሌሎች ተቋማት በተሻለ መስራት ተችሎአል፡፡ የህክምና ስነምግባርን በተመለከተም ዶክመንት እየተዘጋጀ ነው፡፡ እነዚህንና ሌሎች ጠቃሚ ስራዎች በማህበሩ እየተሰሩ በመሆናቸው እና የተሰሩም በመኖራቸው ማህበረሰቡን በበቂ ሁኔታ ለማገልገል ዝግጁ ነን ማለት ይቻላል፡፡ ወደፊትም የማህበሩ አባላት በተሰለፍንባቸው የተለያዩ መስኮች የተሻለ ስራ በመስራት ህብረተሰቡን በተሻለ ሁኔታ ማገልገል ይጠበቅብናል ብዬ አምናለሁ ብለዋል ዶ/ር ደረጀ ንጉሴ፡፡››

Read 2278 times