Saturday, 12 May 2012 09:00

ቢበር የቢዝነስ ኢምፓየር መምራት ጀምሯል

Written by  ግሩም ሠይፉ
Rate this item
(0 votes)

ጀስቲን ቢበር ገና በ18 ዓመቱ ስኬታማ የቢዝነስ ኢምፓዬር በመገንባት እየመራ መሆኑን የዘ ቢዝነስ ኢንሳይደር ሃታታ አመለከተ፡፡ ዘ ቢዝነስ ኢንሳይደር የጀስቲን ቢበርን ኩባንያዎች የሚያንቀሳቅሱ ከፍተኛ የስራ ሃላፊዎችን በማነጋገር ባጠናቀረው ሀተታ፤ ካናዳዊው ታዳጊ አርቲስት በሙዚቃው ብቻ ሳይሆን በኢንቨስትመንቱም ስኬታማ እየሆነ ነው ብሏል፡፡ ጥሬ ሃብቱ 105 ሚሊዮን ዶላር እንደሚደርስ የሚነገርለት ጀስቲን ቢበር፤ ዘንድሮ በፎርብስ መፅሄት በተሰራው የዓለም ተፅእኖ ፈጣሪ ዝነኞች የደረጃ ሰንጠረዥ፤ በሌዲ ጋጋና በኦፕራ ብቻ ተበልጦ በ3ኛ ደረጃ የሚገኝ ነው፡፡

በአንድ ምሽት ለሚሰራው የሙዚቃ ኮንሰርት 600ሺ ዶላር የሚከፈለው ቢበር፤ በትዊተር ድረገፁ 21 ሚሊዮን ተከታታዮች ሲያፈራ በፌስ ቡክ አድራሻው ደግሞ ከ41 ሚሊዮን በላይ ወዳጆች ያለው መሆኑን የጠቀሰው “ዘ ቢዝነስ ኢንሳይደር”፤ ይህም በመላው ዓለም ያለውን ተወዳጅነትና ተፈላጊነት እንደጨመረለት አብራርቷል፡፡ ጀስቲን ቢበር ከሁለት ዓመት በፊት የሰራውና የህይወት ታሪኩን የሚያሳየው “ኔቨር ሴይ ኔቨር” የተባለው ፊልሙ፤ በዓለም ዙርያ ከ100 ሚሊዮን ዶላር በላይ ገቢ ማስገኘቱን ያመለከተው “ዘ ቢዝነስ ኢንሳይደር”፤ በ120 ሚሊዮን ዶላር ካፒታል የሚያንቀሳቀሰው የሽቶ አምራች ኩባንያም ለስኬታማነቱ ትልቅ አስተዋፅኦ እንዳበረከተለት ጠቅሷል፡፡

 

 

 

Read 2082 times Last modified on Saturday, 12 May 2012 09:04