ድርጅቱ በዘጠኝ ወራት 20ሺህ ብር የሚያወጡ መፃሕፍት መሸለሙንና ባላቸው አነስተኛ ቤተመፃሕፍት ብዙ አንባቢ አለመኖሩ አሳስቧቸው ሽልማቱን እንዳቀዱና ከከተማው ወጣቶችና ስፖርት ጽሕፈት ቤት ጋር በጋራ እንደሚሰሩም ለማወቅ ተችሏል፡፡
ጌት ፈርኒቸር እና እንጨት ሥራ ድርጅት ያዘጋጀውና መጽሐፍ በማንበብ የዝግጅቱ መግቢያ የሚገኝበት የእግር ኳስ ውድድር ዛሬ በዓለምገና ከተማ ይጠናቀቃል፡፡ በአራት ዙር የተካሄደው ውድድር አሸናፊዎች “አለምገና ታነባለች” በሚል በጐ ሃሳብ የሚሸለሙት መጽሐፍ እንደሆነ የድርጅቱ ባለቤትና ሥራ አስኪያጅ አቶ ጌቱ በቀለ ለዝግጅት ክፍላችን ገልፀዋል፡፡
ድርጅቱ በዘጠኝ ወራት 20ሺህ ብር የሚያወጡ መፃሕፍት መሸለሙንና ባላቸው አነስተኛ ቤተመፃሕፍት ብዙ አንባቢ አለመኖሩ አሳስቧቸው ሽልማቱን እንዳቀዱና ከከተማው ወጣቶችና ስፖርት ጽሕፈት ቤት ጋር በጋራ እንደሚሰሩም ለማወቅ ተችሏል፡፡