Error
  • JUser: :_load: Unable to load user with ID: 62
Saturday, 14 April 2012 12:43

ከባትማን ፊልም የመጨረሻ ክፍል ከፍተኛ ገቢ ይጠበቃል

Written by 
Rate this item
(0 votes)

በባትማን አፈታሪክ ላይ ተመስርተው ከሚሰሩ ተከታታይ ፊልሞች አንዱ የሆነው “ዘ ዳርክ ናይትስ ራይዝስ” ከፍተኛ ገቢ ሊገኝበት እንደሚችል ተገመተ፡፡ በዲያሬክተር ክሪስቶፈር ኖላን ከተሰሩት የባትማን ፊልሞች ሶስተኛውና የመጨረሻ ክፍል እንደሚሆንም ተገልጿል፡፡ ከሦስት ወር በኋላ እንደሚመረቅ የሚጠበቀው ፊልሙ፤ ለዕይታ ለሚበቃበት የመጀመርያ ሳምንት በመላው ዓለም እስከ 260 ሚ. ዶላር ያስገኛል ተብሏል፡፡ በአይማክስ ካሜራ ተሰርተው ለእይታ በቀረቡ ፊልሞች የመጀመርያ ሳምንት ገቢ 242 ሚ. ዶላር በማስገባት ክብረወሰን የያዘው “አቫታር” ነበር፡፡

ባለፉት ስምንት ዓመታት በክሪስቶፈር ኖላን ተሰርተው ለእይታ የበቁት ሁለት ክፍል የባትማን ፊልሞች “ባትማን ቢጊንስ” እና “ዘ ዳርክ ናይት” የተባሉት ሲሆኑ የመጀመርያው በ150 ሚ. ዶላር በጀት ተሰርቶ በአጠቃላይ 372 ሚ. ዶላር ሲገኝበት በ185 ሚሊዮን ዶላር የተሰራው ከ1 ቢሊዮን ዶላር በላይ ዓለም አቀፍ ገቢ እና 16 ሚሊዮን የዲቪዲ ሽያጭ አግኝቷል፡፡ ሌጀንዳሪ ፒክቸርስ እና ዋርነር ብሮስ በትብብር የሚሰሩት ሦስተኛው “ዘ ዳርክ ናይት ራይዝስ” በአጠቃላይ የሚፈጀው ወጪ 250 ሚ. ዶላር እንደሚደርስ ኤልኤ ታይምስ ጠቁሟል፡፡ የፊልሙ መሪ ተዋናዮች ክርስትያን ቤል እና ኬሲ አፍሌክ ሲሆኑ ጋሪ ኦልድ ማን፤ ማይክል ኬንና ሞርጋን ፍሪማን በረዳት ተዋናይነት ይሳተፉበታል፡፡ ፊልሙን በህንድ፤ በለንደን፤ በግላስኮው፤ በኒውዮርክ ፤ በኒውጀርሲ እና በፒትስበርግ በመዘዋወር የቀረፀው ክሪስቶፈር ኖላን፤ የምስል ጥራቱን በከፍተኛ ደረጃ ለማሳደግ፣ ውዶቹን የአይማክስ ካሜራዎች እንደተጠቀመ ለማወቀ ተችሏል፡፡

 

 

 

Read 1834 times Last modified on Saturday, 14 April 2012 12:45