ርዕስ የለሽ ጽሕፈት
ውል አልባ ምዕራፍ
የምገርፈው በሬ
የሚጮኸው ጅራፍ
ያገር ደጅ ስጠና
ተከፈተ በራፍ፡፡
ክፋት ላይ ስተኩስ
ቅንነት ተመታች
ለተኩላ ባለምኩት
እርግብ በ’ራ ገባች
እርኩስ መቺ ቀስቴ
ደግ ላይ ተሰካች፡፡
ባላሚ ታላሚ
መሀል ስቶ ገብቶ
የዒላማ ግርዶሽ
ባገር ተንሰራፍቶ
አልሞ ለመምታት
አልተቻለም ከቶ፡፡
ከምሥጋና ጋር
ሳምሶን ጌታቸው ተ/ሥላሴ
Published in
የግጥም ጥግ