በመቅዲ ፕሮዳክሽን የሚቀርበው ዝግጅት፣ የአየር ሰዓቱን በነፃ ማግኘቱንና ከቴሌቪዥን ጣቢያው ጋር 50% የማስታወቂያ ገቢ መጋራት በሚል እንደተስማሙ የገለፀችልን የፕሮዳክሽኑ ፕሮጀክት ሥራ አስኪያጅ ወይዘሪት ፈይዛ ሀይሩ፤ ለቀጣይ ሦስት ወራት የሚሆነው ዝግጅት ቀረፃ በአዲስ አበባው ኢንተርኮንቲነንታል ሆቴል መጠናቀቁን ለአዲስ አድማስ ጋዜጣ ገልፃለች፡፡ በዝግጅቱ መክፈቻ የመጀመሪያ ሳምንት አርቲስት አብርሃም ወልዴ፣ በሁለተኛው የሀበሻ ካፒታሉ አቶ እስክንድር ደስታ፣ በሦስተኛው የንግድ ምክር ቤቷ የመጀመሪያዋ ሴት ፕሬዚዳንት ወይዘሮ ሙሉ ሰሎሞን እንግዶች መሆናቸውንም ለማወቅ ተችሏል፡፡