በሙዚቃ ስራው 20 ዓመታትን ያስቆጠረው አሸር፤ ከሁለት ዓመት በፊት ለገበያ እስካበቃው “ራይሞንድ ቨርሰስ ራይሞንድ” የተባለ 6ኛ አልበሙ ድረስ በዓለም ዙርያ 65 ሚሊዮን ቅጂዎችን ሸጧል፡፡ አሸር ሰሞኑን ከእንግሊዛዊቷ ድምፃዊት አዴል ጋር ሙዚቃ መስራት መፈለጉን የተናገረ ሲሆን “ኮንፌሽንስ” በተባለ አልበሙ በአመት ውስጥ በሰሜን አሜሪካ ገበያ ከ10 ሚሊዮን በላይ ቅጂዎችን በመሸጥ ያስመዘገበውን ክብረወሰን ለመስተካከል አቅም ያላት አርቲስት መሆኗንም መስክሮላታል፡፡