Error
  • JUser: :_load: Unable to load user with ID: 62
Saturday, 10 March 2012 11:05

የግጥም ጥግ

Written by 
Rate this item
(3 votes)

 

ሐዘኔ
ሌት ቀኑን ሲወርሰው .. ዠንበሯ ስትሞት፤
ብርሃንና ጸዳል … ቀለምና ውበት፤
ተፋዘው ሳያቸው
በጨለማው ዳፍንት …
ባር ባር ይላል ሆዴ … ያዝናል የኔ ስሜት …
ግና ከዚህ በላይ … ግናም ከዚህ በላይ
ነፍሴን የሚጨንቃት … ልቤ ሚሸበረው፤
ቀኑ ሲጨላልም፤ ንጋት እንደሌለው፤
ጥቁር ከል ደርቦ
ልክ እንደ ጨለማው … ይሄን ቀን ሳየው ነው …
ቀኑ በጨለመ … የማይነጋ መስሎት
ነገም ሌላ ቀን ነው ለተሳነው … ማለት
ተስፋው ለሞተበት፡፡
ታደሠ ለገሠ (ሐዋሳ)

ሐዘኔ

ሌት ቀኑን ሲወርሰው .. ዠንበሯ ስትሞት፤

ብርሃንና ጸዳል … ቀለምና ውበት፤

ተፋዘው ሳያቸው

በጨለማው ዳፍንት …

ባር ባር ይላል ሆዴ … ያዝናል የኔ ስሜት …

ግና ከዚህ በላይ … ግናም ከዚህ በላይ

ነፍሴን የሚጨንቃት … ልቤ ሚሸበረው፤

ቀኑ ሲጨላልም፤ ንጋት እንደሌለው፤

ጥቁር ከል ደርቦ

ልክ እንደ ጨለማው … ይሄን ቀን ሳየው ነው …

ቀኑ በጨለመ … የማይነጋ መስሎት

ነገም ሌላ ቀን ነው ለተሳነው … ማለት

ተስፋው ለሞተበት፡፡

ታደሠ ለገሠ (ሐዋሳ)

 

Read 3840 times