Monday, 15 August 2016 09:25

ሃሳብዎን በ“ነፃነት” ይግለጹ!!

Written by 
Rate this item
(17 votes)

1- ዘንድሮ ኢህአዴግ ከየአቅጣጫው መጠነ-ሰፊ ህዝባዊ
ተቃውሞን እያስተናገደ ነው፡፡ ምናልባት በተቃውሞው
ተማርሮ፤ “ሥልጣን በቃኝ፤ አገሪቱን ተረከቡኝ” ቢል
ምን ይከሰታል?
ሀ) የተዓምር አገር ስለሆነች ምንም አይከሰትም!
ለ) ወላድ በድባብ ትሂድ፤ ደግሞ ስልጣን
ለመረከብ!
ሐ) የተቃዋሚዎች የሥልጣን ሽኩቻ ይቀጥላል!
መ) የማይመስል ነገር ለሚስትህ አትንገር!
ሠ) ባለቤቱ ሰፊው ህዝብ ይረከባላ!
2- የኢህአዴግ አመራሮች፤ ዱብዕዳ በሆነባቸው የህዝብ
ተቃውሞና የባህርይ ለውጥ የተነሳ (ከቻይነት ወደ
እምቢተኝነት!) ምን የሚያጉተመትሙ ይመስልዎታል?
ሀ) ለካስ መንግስቱ፤ “ይሄ ህዝብ ወርቅ ሲያነጥፉለት
ፋንድያ ነው ይላል” ያለው ወዶ አይደለም!!
ለ) በህዝብ ላይ እንደፈፀምነው በደል፣ተቃውሞ
ሲያንሰን ነው!
ሐ) ሥልጣን እንደሆነ ነፍጠኛ እጅ አይገባትም!
መ) ድምጹን ሰጥቶን፣ ፊት ነሳን!
ሠ) ከእንግዲህ ህዝብን ማመን አስሮ ነው!
3- ለወቅቱ ፖለቲካዊ ቀውስና አለመረጋጋት
መፍትሄው ምንድን ነው ይላሉ?
ሀ) ጸሎትና ምህላ!
ለ) ኳሷ በመንግስት እግር ሥር ናት!
ሐ) ለተቃዋሚዎች ሥልጣን ማጋራት!
መ) ውይይትና እርቀ ሰላም!
ሠ) እንኳን እኔ መንግስትም አያውቀው!
4- በአገራችን የሚከሰቱ ፖለቲካዊ ችግሮች የሰው
ህይወት ሳያልፍ፣ በዲሞክራሲያዊ መንገድ
የማይፈቱት ለምንድን ነው?
ሀ) ዲሞክራሲ ሂደት ነው!
ለ) እልኸኝነታችንና ግትርነታችንስ!
ሐ) ይሄን ሊመልስ የሚችለው ኢህአዴግ ብቻ ነው!
መ) ሰዎች፤ የዘራነውን ነው የምናጭደው!
ሠ) እኔም ግራ የሚገባኝ እሱ ነው!
5- አገር በተቃውሞና ግጭት ስትታመስ፣ምሁራኑ
ድምጻቸውን ያጠፉት ለምንድን ነው?
ሀ) ድሮስ መች ድምጽ ነበራቸው!
ለ) እንዲተነፍሱ ማን ዕድል ሰጣቸው!
ሐ) ጎመን በጤና ብለው ይሆናል!
መ) አ ንድም ግ ዴለሽነት አ ሊያም አ ድርባይነት ነው!
ሠ) Boycott Politics ብለው ሊሆን ይችላል! (N.B- ከተሰጡት ምርጫዎች ውስጥ ለእርስዎ
የሚስማማ መልስ ከሌለ፣
የራስዎትን ምርጫ የማካተት መብትዎ የተጠበቀ ነው!!!)




Read 3672 times