ድርጅቱ አዲሱን ምርት አስመልክቶ ባለፈው ሐሙስ በኢትዮጵያ ሆቴል በሰጠው ጋዜጣዊ መግለጫ ላይ አቶ ዳዊት ደስታ እንደተናገሩት፤ እነዚህ ምርቶች ቀደም ሲል ከውጭ አገራት በከፍተኛ የውጭ ምንዛሪ ወደ አገር ውስጥ ይገቡ የነበረ ቢሆንም አሁን ግን እነዚህኑ ልዩ ትራሶች በአገር ውስጥ በማምረት የውጭ ምንዛሪውን ለማስቀረት መቻሉን ጠቁመዋል፡፡ ትራሱ የጭንቅላት፣ የአንገትና የትራስን ቅርፅ ተከትሎ እንዲደግፍ ተደርጐ በልዩ ሁኔታ መሠራቱን የገለፁት አቶ ዳዊት፤ በመኝታ ወቅት ጭንቅላታችን፣ አንገታችን፣ ትከሻችንና ህብለ ሰረሰራችን ትክክለኛውን ቅርፅ ይዞ እንዲደላደል በማድረግ ከበርካታ ህመሞች ሊከላከል ይችላል ብለዋል፡፡
ደንገል ኃ.የተ.የግ.ማህበር ቀደም ሲል የተለያዩ የህፃናትና የእርጉዝ እናቶችን ምቾት ለመጠበቅ የሚያስችሉ ትራሶችን ሲያመርት የቆየ ድርጅት ነው፡፡