Print this page
Saturday, 30 January 2016 11:55

የዘላለም ጥግ

Written by 
Rate this item
(6 votes)

• ጥያቄ የሚጠይቁ ሰዎች አያስፈሩኝም፡፡ እኔን
የሚያስፈሩኝ መልስ ለመስጠት አሻፈረን
የሚሉት ናቸው፡፡
ጃሶን ባቼታ
- ዓለም አገሬ ናት፤ የሰው ልጆች በሙሉ ወንድሞቼ
ናቸው፤ በጎ መስራት ሃይማኖቴ ነው፡፡
ቶማስ ፓይኔ
- የልጆቼን አይስክሬም 38 በመቶ እየበላሁባቸው
ስለግብር ምንነት አስተምሬአቸዋለሁ፡፡
ኮናን ኦ’ብሪን
- የጣልያን ምግብ የመብላት ችግሩ ከአምስት
ወይም ከስድስት ቀን በኋላ እንደገና ይርብሃል፡፡
ጆርጅ ሚለር
- በድጋሚ ሚስት ከማግባት ይልቅ የማልወዳትን
ሴት ፈልጌ አንድ የመኖሪያ ቤት እሰጣታለሁ፡፡
ሮድ ስቲዋርት
- ምንጊዜም ከጨለምተኛ ሰው ገንዘብ ተበደር፡፡
ገንዘቡ ይመለስልኛል ብሎ አይጠብቅም፡፡
ኦስካር ዋይልድ
- ችግሮችህን ፈፅሞ ለማንም አትንገር፡፡ 20 በመቶ
ያህሉ ግድ የላቸውም፤ 80 በመቶው ደግሞ
በችግር በመጠመድህ ደስተኞች ናቸው፡፡
ሎዮ ሆልትዝ
- ትዳር ከመያዜ በፊት ስለልጆች አስተዳደግ
ስድስት ኃልዮቶች ነበሩኝ፤ አሁን ስድስት ልጆች
አሉኝ፤ ነገር ግን ምንም ኃልዮት የለኝም፡፡
ጆን ዊልሞት
- የሰውን አዕምሮ ከመልሶቹ ይልቅ በጥያቄዎቹ
መመዘን ይቀላል፡፡
ፒሬ ማርክ
- ሁሉንም ውደድ፤ ጥ ቂቶችን እመን፤ ማ ንም ላ ይ
መጥፎ አታድርግ፡፡
ዊሊያም ሼክስፒር
- ሃቁን የምትናገር ከሆነ ምንም ነገር ማስታወስ
የለብህም፡፡
ማርክ ትዌይን
- ዘመዶቻችንን እግዚአብሔር ሰጥቶናል፤
እግዚአብሔር ይመስገን ጓደኞቻችንን መምረጥ
እንችላለን፡፡
ኢቴል ሙምፎርድ
- ጋራዥ ውስጥ መቆም መኪና እንደማያሰኝህ ሁሉ
ቤተክርስቲያን መሄድም ክርስቲያን አያሰኝህም፡፡
ቢሊ ሰንዴይ

Read 4065 times
Administrator

Latest from Administrator