Saturday, 12 December 2015 11:28

የግጥም ጥግ

Written by 
Rate this item
(2 votes)

እዬዬ ማይገልፀው
ምን ይበል አባቷ
ምን ትበል እናቱ
ለወግ ያሰበችው ሲቀጠፍ በከንቱ
ምን ይላል ወገኔ
ጉንጬ በእምባ ሲርስ - አንጀቴ ሲታጠፍ
ኮትኩቼ ያበበው
መዐዛው ሚስበው
የማታ አበባዬ በአጭሩ ሲቀጠፍ
ያቺ ምስኪን እናት
የማታዋን ሳታውቅ በጠዋት ተነስታ
ከዛሬው ወጋገን የነገውን አይታ
ጨርሳ አትሸኘው
ለአይኗ እንኳ ሳስታ
በደንብ እንዳትስመው
ያንን ስርጉድ ጉንጩን
ብሉኝ ብሉኝ ሚለው
ሞልቶ-ትርፍ ፈገግታ
የጠዋት ፀሎቷ - ጅምር በረከቷ - በእንባዋ
 ሲታበስ
የፀበል ማቆርያ - የህመም
ብርታቷ - ሲሰበር ላይታፈስ
እንዴት አሟት ይሆን
ልቧ ውስጧ ሲሞት
ያልጠና አጥንቱ - ያልገራ ጅማቱ - ጎማ
ሲበትነው
ያልቦረቀች ነፍሱ - ጅምር ለጋነቱ - ሲቃ
ሲፈትነው
እህህ አይገልፀው
እዬዬ አይክሰው
እምባዋን ረጭታው -
ከመብሰክሰክ በቀር - ምን ታደርገዋች
አንዴ ፈሷል ነገር - ዳግመኛ አትወልደው -
በምን ታፍሰዋለች
(መታሰቢያነቱ ሰሞኑን በአዲስ አበባ ከትምህርት ቤት ሲመለሱ በመኪና አደጋ ህይወታቸውን ላጡት ህጻናት ይሁንልኝ፡፡)
(ከዘም ዛሚ ፌስቡክ)

Read 3325 times