የተለያዩ የስፖርት መሥሪያ መሳሪያዎችን አምርቶ ለገበያ በማቅረብ የሚታወቀው የላይፍ ፊትነስ እናት ድርጅት ብራንዝዊክ ኮርፖሬሽን በዕድሜ ለገፉ ሰዎች ጠቃሚ የሆኑ የስፖርት መስሪያ ዕቃዎችን በማምረት የሚታወቀውን ሳይፈት የተባለ ድርጅት በመግዛት የድርጅቱ አካል ማድረጉን አስታወቀ፡፡
የላይፍ ፊትነስ ፕሬዚዳንት ሚስተር ክሪስ ላውሶን እንደገለፁት ላይፍ ፊትነስ ሳይፊትን መግዛቱ ቁጥራቸው በፍጥነት እያደገ ያለውን በዕድሜ የገፉ ወገኖችን ሊረዳ የሚችል ምርት ለማቅረብ ያስችለናል ብለዋል፡፡
ይህም ድርጅቱ ጡረተኞች እንዲሁም ልዩ እርዳታና እንክብካቤ የሚያሰፈልጋቸው ወገኖች ለሚገለገሉባቸው ቦታዎች፣ ለአረጋውያን መንከባከቢያ ተቋማት፣ ለማረሚያ ቤቶችና የተአድሶ ሥፍራዎች አስፈላጊ የሆኑ ምርቶችን የስፖርት መስሪያ ለማቅረብ እንደሚያስችላቸው ገልፀዋል፡፡
ላይፍ ፊትነስ ለጂም የሚሆኑ የአካል ብቃት እንቅስቃሴ ምርቶች፣ የመዝናኛ ጠረጴዛዎች እንዲሁም የተለያዩ ዕቃዎች አምርቶ ለገበያ በማቅረብ ቀዳሚ የሆነ ድርጅት ነው፡፡
Published in
ዋናው ጤና
Latest from Administrator
- የእስራኤል እና የኢራን ፍጥጫ
- Insights on Israel's Response: Interview with Mr. Tomer Bar-Lavi, Chargé d’Affaires at the Embassy of Israel to Ethiopia
- Barr, a vocal Trump critic, says he will ‘support the Republican ticket’ in November
- Iran president warns of ‘massive’ response if Israel launches ‘tiniest invasion’
- "አልሞቷል" ፊልም ዛሬ በዓለም ሲኒማ ይመረቃል