Print this page
Saturday, 07 November 2015 10:18

የግጥም ጥግ

Written by 
Rate this item
(16 votes)

የመንፈስ ዘውድ
ነፍስ የራስዋን ዓለም መርጣ እንደሰየመች
ማንም እንዳይገባ በርዋን ጠረቀመች፣
ከርስዋም ቅዱስና ብዙሃናዊ ዓለም
ሠርገው ለሚገቡ ምንም ሽንቁር የለም፡፡
* * *
ሳትንቀሳቀስም ታያለች ባርምሞ
ታችኛው በርዋ ላይ ሠረገላ ቆሞ፤
ሳትንቀሳቀስም ታያለች ንጉሱን
ከግሮችዋ ምንጣፍ ስር ወድቆ ማጐንበሱን፡፡
* * *
እኔም አውቃታለሁ ከወዲያኛው ሀገር
አንድ ነገር ብቻ መርጣ በቁም ነገር፣
ከዚያ የትኩረትዋን በር፣ የልቧን ጥሞና
እንደቋጥኝ ዓለት ጥርቅም አርጋ ደፍና፡፡
ኤሚሊ ዲክንሰን
ሚክሎልና ፍልስፍና ትርጉም በጁዲት ሙሉጌታ

Read 4306 times
Administrator

Latest from Administrator