Saturday, 07 November 2015 10:18

የግጥም ጥግ

Written by 
Rate this item
(16 votes)

የመንፈስ ዘውድ
ነፍስ የራስዋን ዓለም መርጣ እንደሰየመች
ማንም እንዳይገባ በርዋን ጠረቀመች፣
ከርስዋም ቅዱስና ብዙሃናዊ ዓለም
ሠርገው ለሚገቡ ምንም ሽንቁር የለም፡፡
* * *
ሳትንቀሳቀስም ታያለች ባርምሞ
ታችኛው በርዋ ላይ ሠረገላ ቆሞ፤
ሳትንቀሳቀስም ታያለች ንጉሱን
ከግሮችዋ ምንጣፍ ስር ወድቆ ማጐንበሱን፡፡
* * *
እኔም አውቃታለሁ ከወዲያኛው ሀገር
አንድ ነገር ብቻ መርጣ በቁም ነገር፣
ከዚያ የትኩረትዋን በር፣ የልቧን ጥሞና
እንደቋጥኝ ዓለት ጥርቅም አርጋ ደፍና፡፡
ኤሚሊ ዲክንሰን
ሚክሎልና ፍልስፍና ትርጉም በጁዲት ሙሉጌታ

Read 4269 times