በቅርቡ በሳዑዲ አረቢያ በሃጂ ስነስርአት ወቅት በተፈጠረ መጨናነቅ ህይወታቸውን ያጡ ኢትዮጵያውያን ቁጥር 47 መድረሱን የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት ገልጿል፡፡
ባለፈው መስከረም 13 ቀን 2008 በሳዑዲ አረቢያ ሚና አካባቢ በደረሰ አደጋ ከ1ሺህ በላይ የተለያዩ ሀገር የሃይማኖታዊ ስነ ስርአቱ ተሳታፊዎች ህይወታቸውን ባጡበት ወቅት ኢትዮጵያውያን ላይ አደጋ ስለመድረሱ ወዲያው ማወቅ ያልተቻለ ሲሆን ከቀናት በኋላ 2 ኢትዮጵያን ህይወታቸው ማለፉ ተዘግቦ እንደነበርና ኋላም የሟቾች ቁጥር ወደ 31 ማደጉ ይታወቃል፡፡ ከትናንት በስቲያ የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት ቁጥሩ 47 መድረሱንና ተጐድተው ሆስፒታል ገብተው ከነበሩት 26 ኢትዮጵያውያን 24 ተሽሏቸው ከሆስፒታል ሲወጡ፣ 2ቱ ተኝተው ህክምና እየተከታተሉ መሆኑ ታውቋል፡፡
ለሃጅ ስነስርአት ወደ ሳዑዲ አረቢያ ሄደው የነበሩ ከ1ሺህ 100 በላይ አማኞች መመለሳቸውንም ምክር ቤቱ አስታውቋል፡፡ በዘንድሮ የሃጂ ስነስርአት ላይ 10ሺ ኢትዮጵያውያን መሣተፋቸውም ታውቋል፡፡
Published in
ዜና
Latest from Administrator
- የእስራኤል እና የኢራን ፍጥጫ
- Insights on Israel's Response: Interview with Mr. Tomer Bar-Lavi, Chargé d’Affaires at the Embassy of Israel to Ethiopia
- Barr, a vocal Trump critic, says he will ‘support the Republican ticket’ in November
- Iran president warns of ‘massive’ response if Israel launches ‘tiniest invasion’
- "አልሞቷል" ፊልም ዛሬ በዓለም ሲኒማ ይመረቃል