ንግድ ባንክ የአስቀማጭ ደንበኞች ቀንን የፊታችን ማክሰኞ የሚያከብር ሲሆን በ”ይቆጥቡ ይሸለሙ” የተሸለሙ የአዲስ አበባ እድለኞች በእለቱ ሽልማታቸውን ይረከባሉ፡፡
ባንኩ የአስቀማጭ የደንበኞች ቀንን ለ4ኛ ጊዜ የሚያከብር ሲሆን የባንኩ የቦርድ አባላትና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች እንዲሁም ተሸላሚዎች ይታደማሉ ተብሏል፡፡ ፕሮግራሙ ከ11 ሰዓት ጀምሮ በሂልተን ሆቴል ቦልሩም አዳራሽ እንደሚካሄድ የጠቆመው ባንኩ፣ የ4ኛ ዙር “የይቆጥቡ ይሸለሙ” ፕሮግራምና 1ኛ ዙር የወጭ ምንዛሬ ግኝት ማበረታቻ ፕሮግራም ላይ አሸናፊ የሆኑ የአዲስ አበባ ዲክትሪክት እድለኞችም ሽልማታቸውን ይረከባሉ፡፡ ቀደም ሲል ባንኩ በሁለቱም የሽልማት ፕሮግራሞቹ ከ2 ሺህ በላይ አሸናፊዎችን ስም ዝርዝር ይፋ ማድረጉ የሚታወስ ነው፡፡ ቁጠባን ለማበረታታት ባንኩ ባለፉት አራት የ “ይቆጥቡ ይሸለሙ” ዙር ፕሮግራሞች በርካቶችን ተጠቃሚ ማድረጉንና ቆጣቢ ደንበኞችንም እያበራከተ መሆኑን ለማወቅ ተችሏል፡፡