Monday, 31 August 2015 08:50

ኦባማ በአዲስ አበባ ቆይታቸው ለሆቴል 1.3 ሚ. ዶላር ከፍለዋል

Written by 
Rate this item
(3 votes)

     ከአንድ ወር በፊት ኢትዮጵያን የጎበኙት የአሜሪካው ፕሬዚዳንት ባራክ ኦባማ በአዲስ አበባ በነበራቸው የሁለት ቀናት ቆይታ ለሆቴል 1.3 ሚ. ዶላር ማውጣታቸውን ዊክሊ ስታንዳርድ ድረገጽ ከትናንት በስቲያ ዘገበ፡፡
ኦባማ እና አብረዋቸው የመጡ የደህንነትና የልኡካን ቡድን አባላት በአዲስ አበባ በሚገኙ አራት ሆቴሎች ማረፋቸውን የጠቆመው ዘገባው፣ በሁለት ቀናት ቆይታቸው ለሆቴሎቹ በድምሩ 1.3 ሚሊዮን የአሜሪካ ዶላር መከፈሉን ገልጿል፡፡የጉብኝቱ አዘጋጆች በመጀመሪያ ከሂልተን ሆቴል ጋር የ412ሺ 390 ዶላር ውል መፈጸማቸውንና በቀጣይም ከኢሊሌ ኢንተርናሽናል ሆቴል ጋር የ246ሺ 877 ዶላር፣ ከካፒታል ሆቴልና ስፓ ጋር ደግሞ የ178ሺ 433 ዶላር ውል መፈጸማቸውን የጠቀሰው ዘገባው፤ በመጨረሻም ከሸራተን አዲስ ሆቴል ጋር የ488ሺ 141 ዶላር ስምምነት መፈጸማቸውን ጠቁሟል፡፡የልኡካን ቡድኑ አባል የሆነ አንድ የዋይት ሃውስ ፎቶ ግራፍ አንሺን እማኝነት በመጥቀስ ዘገባው እንዳለው፣ ኦባማ በሁለት ቀናት ቆይታቸው ያረፉት በሸራተን አዲስ ሆቴል እንደነበር መረጋገጡንም ዘገባው አክሎ ገልጧል፡

Read 4052 times