Monday, 31 August 2015 08:49

በላቀ ውጤት ለዩኒቨርሲቲ ያለፉ ሴት ተማሪዎች አሸኛኘት ተደረገላቸው

Written by 
Rate this item
(1 Vote)

     በአዲስ አበባ ከተማ ውስጥ ከሚገኙ የተለያዩ ትምህርት ቤቶች ከፍተኛ ነጥብ አምጥተው ዩኒቨርሲቲ ለገቡ ከ2 ሺ 500 በላይ ሴት ተማሪዎች ትላንት የሽኝት ፕሮግራም ተደረገ፡፡
“ዘር ኢትዮጵያ” በተባለ ድርጅት በአፍሪካ ህብረት አዳራሽ በተካሄደው ፕሮግራም፤ በተለያዩ የሥራ መስኮች ስኬታማ የሆኑ ሴቶች ለተማሪዎቹ ከህይወት ልምድና ተሞክሮአቸው አካፍለዋል፡፡
ሴት ተማሪዎቹ በዩኒቨርሲቲ ቆይታቸው የሚገጥሟቸውን በርካታ ችግሮችና መሰናክሎች በአሸናፊነት ለመወጣት የዓላማ ፅናት ሊኖራቸው እንደሚገባ የተነገራቸው ሲሆን ለዚህም ከወዲሁ ራሳቸውን ማዘጋጀት እንደሚኖርባቸው ምክር ተለግሰዋል፡፡ለወጣት ተማሪዎቹ የህይወት ልምድና ተሞክሮአቸውን ካጋሩ ስኬታማ ሴቶች መካከል የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የኢንፎርሜሽን ሲስተም ምክትል ፕሬዚዳንት ወ/ሮ መሊካ በድሪ፣ በመከላከያ ሚኒስቴር የስነ ምግባር መከታተያ ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር ብ/ጄ ዘውዱ ኪሮስና  የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ኮርፖሬሽን ዋና ሥራ አስፈፃሚ ኢንጂነር አዜብ ወርቁ ይጠቀሳሉ፡ሽኝት የተደረገላቸው ሴት ተማሪዎች በአዲስ አበባ ትምህርት ቢሮ በኩል የተመረጡ መሆናቸው ታውቋል፡፡
የፕሮግራሙ አዘጋጅ “ዘር ኢትዮጵያ”፤ አራት መቶ ሴትና አንድ መቶ ወንድ ተማሪዎችን በየወሩ 200 ብር ድጋፍ እያደረገ ትምህርታቸውን እንዲከታተሉ የሚያበረታታ ሲሆን በቀጣዩ ዓመት ድጋፍ የሚደረግላቸውን ተማሪዎች ቁጥር ወደ  1000 ለማድረስ እቅድ መያዙ ተገልጿል፡፡  

Read 2231 times