Saturday, 11 July 2015 10:50

ዓለም አቀፍ የኦንላይን ሪልእስቴት ኩባንያ ሥራ ጀመረ

Written by 
Rate this item
(0 votes)

    መኖሪያ ቤቶችንና ንብረቶችን በኢንተርኔት መሸጥና መግዛት የሚያስችል ዘመናዊ የግብይት ሥራ
የሚያከናውን “ላሙዲ” የተባለ አለምአቀፍ የኦንላይን ሪልስቴት ኩባንያ ሥራ ጀመረ፡፡ደንበኞች ንብረታቸውን በቀላሉ ለመሸጥና ለመግዛትያስችላቸዋል የተባለው ዘመናዊው የኢንተርኔት መገበያያበኢትዮጵያ ሥራ መጀመሩን አስመልክቶ ከትናንት በስቲያበኩባንያው ቢሮ በተሰጠው ጋዜጣዊ መግለጫ ላይእንደተጠቆመው፤ በአገሪቱ ሪልእስቴቶች ከጊዜ ወደ ጊዜእያደጉና እየሰፉ የመጡ ሲሆን በዚህም የተነሳ ደንበኞችስለ መኖሪያ ቤቶች በቂና ጥልቀት ያለው መረጃ ለማግኘትየሚችሉበት መንገድ በስፋት ሊኖር ይገባል፡፡ ኩባንያውገዢና ሻጭ በኦንላይን ተገናኝተው መኖሪያ ቤታቸውንናሌሎች ንብረቶች እንዲገበያዩ ያስችላል ተብሏል፡፡ኩባንያው ኢንተርኔት ለማይጠቀሙ ደንበኞቹዳያል 4 ሆም የተሰኘ የስልክ አገልግሎት የሚሰጥ ሲሆንደንበኞች ስልክ በመደወል የሚፈልጉትን መኖሪያ ቤትበተመለከተ ዝርዝር መረጃና አገልግሎት እንደሚያገኙተገልጿል፡፡ እስካሁን ከተለያዩ ሪል እስቴቶችና ወኪሎችያገኛቸውን 20ሺ ገደማ መኖርያ ቤቶችና ንብረቶችበድረገፁ ላይ እንዳቀረበም ለማወቅ ተችሏል፡፡ላሙዲ በተለያዩ ዘርፎች የኦንላይን አገልግሎትየሚሰጥ ሲሆን በኬንያ፣ ታንዛኒያ፣ ናይጀሪያ፣ ጋና፣ኡጋንዳና ሩዋንዳ ቢሮዎቹን ከፍቶ ተመሳሳይአገልግሎቶችን በመስጠት ላይ የሚገኝ ኩባንያ እንደሆነታውቋል፡፡

Read 1591 times